WORK IN PROGRESS! NOT FINALIZED YET
78-103 የኢየሱስ ልደት እና አገልግሎት
Birth and Ministry of Jesus

በታሪክ 78-103 ፈልግ፡
78. የአጥማቂው ዮሐንስ መወለድ
ሉቃስ 1
ካህኑ ዘካርያስ እና ኤልሳቤጥ እግዚአብሔርን የሚያስደስት ሕይወት የሚኖሩ ባል እና ሚስት ነበሩ። እነርሱም እስከ እርጅናቸው ድረስ ልጅ አልነበራቸውም። አንድ ቀን መልአኩ ገብርኤል ለዘካርያስ በቤተ መቅደስ እያገለገለ ሳለ ተገለጠለት። ዘካርያስ ገብርኤልን ሲያይ በፍርሀት ተንቀጠቀጠ። መልአኩም “አይዞህ፥ አትፍራ! በቅርብ ጊዜ ላንተ እና ለብዙዎች ደስታ የሚሆን ልጅ ትወልዳለህ። ስሙንም ዮሐንስ በለው! እርሱም ሕዝቡን ለአዳኙ ለክርስቶስ መምጣት ልባቸውን ያዘጋጃል” አለው። ዘካርያስም እርሱ እና ሚስቱ ስላረጁ ይህ እንዴት ሊሆን እንደሚችል ጠየቀው። መልአኩም “የነገርኩህን ቃል ስላላመንክ ልጅህ እስኪወለድ ድረስ መናገር አትችልም” አለው። ዘካሪያስም ወዲያውኑ መነገር አቃተው።
ከተወሰኑ ወራት በኋላ ኤልሳቤጥ ልጅን ወለደች። ዘካሪያስም መልአኩ እንደነገረው ስሙን ዮሐንስ አለው። የዚያን ጊዜ እንደገና መናገር ጀመረ።
The Birth of John the Baptiser 
Luke 1
The priest Zechariah and his wife Elizabeth lived a life pleasing to God. They were already old, yet still had no child. But one day the angel Gabriel appeared to Zechariah as he was serving in the Temple. Zechariah trembled with fear when this happened. The angel said to him: “You don’t need to be afraid. Soon you will have a son who will bring joy to you and to many others. You must call him John. He will prepare the hearts of the people for the coming of the promised Saviour.” Following that, Zechariah asked the angel how this could happen since he and his wife were already old. The angel answered: “Because you did not believe what I told you, you will not be able to speak until the birth of your son.” And immediately Zechariah could not speak anymore.
Several months later Elizabeth gave birth to a son and Zechariah named him John, as the angel had told him to. At that time, he started to speak again.

እግዚአብሔር መልአኩን ልኮ ለዘካሪያስ ጸሎቱ እንደተሰማ እና ልጅ እንደሚሰጠው ሲነግረው
መልአኩ የዮሐንስ ስራ ምን እንደሆነ ተናገረ? 
ስራው ለሚመጣው አዳኝ ለክርስቶስ የሕዝቡን ልብ ማዘጋጀት መሆኑን ተናገረ።
79. ገብርኤል ለማርያም ተገለጠ 
ሉቃስ 1
ከተወሰኑ ወራት በኋላ እግዚአብሔር መልአኩ ገብርኤልን ማርያም ወደ ምትባል ሴት ላከው። እርሱም “ጌታ ከአንቺ ጋር ነውና፥ አትፍሪ! ልጅ ትወልጃለሽ። ስሙንም ኢየሱስ ብለሽ ጥሪው። እርሱም የእግዚአብሔርም ልጅ ይባላል። እግዚአብሔርም ለዳዊት እንደገባው ቃል ለዘለአለም ንጉሥ ይሆናል” አላት። ማርያም ገና ያላገባች ልጅ ስለነበረች መልአኩን “እሺ፥ ይህ ግን እንዴት ሊሆን ይቻላል?” ብላ ጠየቀችው። መልአኩም “ይህ የሚሆነው በእግዚአብሔር ኃይል ነው” አላት። ማርያምም በመልአኩ የመጣላትን ቃል በእምነት ተቀበለች።
ከጥቂት ቀኖች በኋላ ወደ ዘመድዋ ወደ ኤልሳቤጥ ሄደች። እዚያም ስትደርስ ስለተደረገላቸው ነገር አብረው እግዚአብሔርን አመሰገኑ።
Gabriel Appears to Mary 
Luke 1
Some months later God sent the angel Gabriel to a woman called Mary. He said to her: “Don’t be afraid, for the Lord is with you. You will give birth to a son. You must name him Jesus. He will be called ‘Son of God’. As God promised to David, he will be king forever.”
Because Mary was not yet married, she responded to the angel, “Yes, okay, but how can this happen?” The angel replied that this would happen by God’s power. And Mary believed and accepted the angel’s message.
A few days later, she went to visit her relative Elizabeth. When she arrived there, they praised God together for what he had done for them.

እግዚአብሔር በመልአኩ በገብርኤል በኩል ማርያም ልጅ እንደምትወልድ ሲነግራት
እግዚአብሔር አንዳንድ ጊዜ እጅግ በጣም አስፈላጊ ነገር በመልአክ በኩል ይናገራል። መልአኩ ለማርያም ምን ነገራት? 
ኢየሱስ የሚባል የእግዚአብሔር ልጅ እንደምትወልድ ነገራት።
80. የኢየሱስ መወለድ
ማቴዎስ 1 + ሉቃስ 2
ማርያም ስለምትወልደው ልጅ በሰማች ጊዜ ዮሴፍ የሚባል እጮኛ ነበራት። ከዮሰፍም ጋር ሳይጋቡ በእግዚአብሔር መንፈስ አረገዘች። መልአክም በሕልም ለዮሴፍ ተገልጦ ማርያም ያረገዘችው በመንፈስ ቅዱስ ኃይል መሆኑን አስረዳው። ስለዚህ ማርያምን የማግባት ሀሳቡን እንዳይተው ተናገረው።
መንግስት የሕዝብ ቁጥር እየመዘገበ ስለነበር፥ ዮሴፍ እና ማርያም ሊመዘገቡ ወደ ቤተልሔም ከተማ ተጓዙ። በቤተልሔም ሳሉ ማርያም ኢየሱስን ወለደች። የሚያርፉበት ቤት ስላላገኙ፥ እንስሶች በሚበሉበት ቦታ በግርግም አስተኛችው። ኢየሱስ በተወለደበት ሌሊት በቅርብ በጎች ሲጠብቁ ለነበሩ እረኞች መልአክ ተገለጠላቸው። እርሱም “አትፍሩ፥ ዛሬ አዳኝ የሆነው ጌታ በቤተልሔም ተወልዶላችኋል” አላቸው። እነርሱም ወደ ቤተልሔም ሄደው ኢየሱስን ከማርያም እና ከዮሴፍ ጋር አገኙት። እርሱንም ስላዩ እጅግ ደስ እያላቸው እግዚአብሔርን አመሰገኑ።
Jesus’ Birth
Matthew 1 + Luke 2
When Mary heard that she would give birth to a son, she was engaged to a man called Joseph. That means she was not married yet when she became pregnant by God’s Spirit. Then an angel appeared to Joseph. He explained to him in a dream that Mary became pregnant by the Holy Spirit and he should not change his mind about marrying her.
Some time later, Joseph and Mary had to travel to the town of Bethlehem to be registered, because the government was counting the people. While they were there, Mary gave birth to Jesus. She laid her son in a food tray in an animal shelter, since they had not found a house to stay in.
During the night that Jesus was born, an angel appeared to shepherds in the field. He said to them, “Don’t be afraid. Today the promised Saviour has been born in Bethlehem.” So they went to Bethlehem and found Jesus together with Mary and Joseph. When they saw him, they rejoiced and praised God.

ኢየሱስ ከተወለደ በኋላ፥ እረኞቹ በፍጥነት ቤተልሔም ደርሰው ሲያዩት
እግዚአብሔር ለሰዎች የላከው አዳኝ ማን ነው?
የተላከው አዳኝ ኢየሱስ ነው።
81. ጠቢባኑ ወደ ኢየሱስ መጡ
ማቴዎስ 2
ጠቢባን የሆኑ ሰዎች በምስራቅ ልዩ ኮከብ ሲወጣ አዩ። በዚህም አዲስ ንጉሥ በእስራኤል እንደተወለደ አስተዋሉ። የተወለደውን ንጉሥ ለማየት ካሉበት ሀገር ተነስተው ከብዙ ጉዞ በኋላ ኢየሩሳሌም ደረሱ። በዚያም “የተወለደውን ንጉሥ የት እናገኘዋለን? ኮከቡን በምስራቅ ሲወጣ አይተን ልንሰግድለት መጥተናል” ብለው ሰዎችን ጠየቁ። የመፀሐፍ ቅዱስ አስተማሪዎች፥ አዳኙ የሚወለደው በቤተልሔም እንደሆነ ነገሯቸው። ከብዙ መቶ ዓመታት በፊት የእግዚአብሔር ነቢያት ይህንን ተናግረው ነበር። ስለዚህ ጠቢባኑ ተነስተው ወደ ቤተልሔም ሄዱ። ኮከቡም እየመራቸው ሲሄዱ፥ ኢየሱስ ያለበት ቤት ሲደርሱ ቆመ። ወደ ቤቱም ሲገቡ ሕፃኑን ኢየሱስን ከእናቱ ከማርያም ጋር አገኙት እና ሰገዱለት። ይዘውለት የመጡትንም ውድ ስጦታዎች ሰጡት።
እግዚአብሔር የነገሥታትን ንጉሥ መምጣት በቃሉ፥ በነቢያት፥ በመላእክት እና በልዩ ኮከብ አስታውቆ ነበር።
The Visit of the Wise Men
Matthew 2
Wise men from the east saw a special star rising. By this they knew that a new king was born in Israel. So they set out from their country to visit the new king and after a long journey arrived in the city of Jerusalem. There they asked the people, “Where can we find the new born king? We have seen his star rise in the east and have come to honour him.” Teachers of the Bible then informed them that the Saviour would be born in Bethlehem. God’s prophets had announced this many hundreds of years before. Based on these words the wise men went to Bethlehem. The star guided them and stopped above the house where Jesus was. When they went inside, they found Jesus with his mother Mary and they bowed down before him. They gave him the precious gifts they had brought.
God made the arrival of the King of Kings known through his word, through prophets, angels and even through a special star.

ጠቢባኑ ሰዎች ኢየሱስን አክብረው ስጦታ ሲሰጡት
ጠቢባኑ ሰዎች ኢየሱስን ባገኙት ጊዜ ምን አደረጉ?
ጠቢባኑ ለኢየሱስ ሰግደው ይዘውለት የመጡትን ስጦታዎች ሰጡት።
82. ስምዖን እና ሐና
ሉቃስ 2
ስምዖን የሚባል የእግዚአብሔር ሰው፥ እግዚአብሔር አዳኙን ኢየሱስን ሳያይ እንደማይሞት ስለተናገረው፥ ለረጅም ጊዜ በእምነት ይጠባበቅ ነበር። አንድ ቀን ዮሴፍ እና ማርያም ከሕፃኑ ከኢየሱስ ጋር ወደ ቤተ መቅደስ ሄዱ። ስምዖንም መንፈስ ቅዱስ ስለመራው ወደ እነርሱ መጥቶ ሕፃኑን ኢየሱስን አቀፈው። ለብዙ ጊዜ የጠበቀውን አዳኝ ስላየ፥ በደስታ እግዚአብሔርን አመሰገነ። እርሱም “ኢየሱስ ለሰዎች ሁሉ ሕይወትን የሚሰጥ ብርሃን ነው” አለ። ቢሆንም ግን የማይቀበሉትም ሰዎች እንደሚኖሩ ተናገረ።
በዚያን ጊዜ አንዲት ሐና የምትባል ነቢይት ደግሞ በቤተ መቅደስ ነበረች። እርሷም ሕፃኑን ኢየሱስን ባየች ጊዜ፥ አዳኝ መሆኑን ለሰዎች እየተናገረች እግዚአብሔርን አመሰገነች።
Simeon and Anna
Luke 2
A man of God named Simeon had been waiting patiently for a long time, because God had told him that he would not die before seeing the Saviour.
One day Joseph and Mary went to the Temple with baby Jesus. Then Simeon came to them, because the Holy Spirit led him. He took Jesus in his arms and thanked God full of joy. He finally saw the Saviour that he had been waiting for for a long time. He said, “Jesus is the light which gives life to all people.” Nevertheless he also said that not everybody would accept him.
At that time there was a prophetess called Anna in the Temple as well. She also praised God when she saw the child and told the people that he is the Saviour.

ስምዖን እና ሐና ስለሕፃኑን በተናገሩት ቃል ማርያም እና ዮሴፍ ሲገረሙ
ኢየሱስ ሕይወት የሚሰጥ ብርሃን የሚሆነው ለማን ነው?
ኢየሱስ ብርሃን የሚሆነው ለሚቀበሉት ሰዎች ሁሉ ነው።
83. ኢየሱስ በ12 አመቱ በቤተ መቅደስ መቆየቱ
ሉቃስ 2፥41-52
በእስራኤል ሀገር በኢየሩሳሌም ከተማ ብቻ ወደሚገኘው ቤተ መቅደስ ሕዝቡ ለዋና በዓላት ይሄዱ ነበር። እንደልማዳቸው ማርያም እና ዮሴፍም የፋሲካን በዓል ለማክበር ሲሄዱ፥ ኢየሱስን በ12 አመቱ ይዘውት ወደ ቤተ መቅደስ ሄዱ። በዓሉ ካለቀ በኋላ፥ ወደ ቤታቸው ረጅሙን ጉዞ መጓዝ ጀመሩ። ኢየሱስ ግን በቤተ መቅደስ እንደቀረ በመጀመሪያ አላወቁም ነበር። ሊፈልጉትም እንደገና ወደ ኢየሩሳሌም ተመለሱ። ከሦስት ቀናትም በኋላ በቤተ መቅደስ ውስጥ አገኙት። በዚያም ከእስራኤል ሕግ አስተማሪዎች ጋር ስለ እግዚአብሔር ቃል ይወያይ ነበር። ሁሉም ስለ እግዚአብሔር ባለው እውቀት ተገረሙ። በመጨረሻም ዮሴፍ እና ማርያም ከኢየሱስ ጋር አብረው ወደ ቤታቸው ተመለሱ።
12 Year Old Jesus in the Temple
Luke 2:41-52
For celebrating their most important holidays Israelites went to Jerusalem, because the only Temple for God was there. Also Mary and Joseph were used to go to Jerusalem every year to celebrate the Passover feast. When Jesus was 12 years old, he went along with them. And after the holiday, they set out on the long journey back home without knowing that Jesus had stayed behind in the Temple. Finally Joseph and Mary returned to Jerusalem to look for him. After three days of searching they found him in the Temple. There he was discussing God’s Word with the teachers of Israel’s law. Everyone was amazed at the knowledge Jesus had about God. After Joseph and Mary found him, he went back home with them.

ኢየሱስ ገና ልጅ ሆኖ ሳለ ስለ እግዚአብሔር ቃል ሲጠይቅ እና ሲመልስ
ኢየሱስን የሰሙት ሰዎች ለምን ተገረሙ?
ኢየሱስ ስለ እግዚአብሔር ባለው እውቀት ተገረሙ።
84. የኢየሱስ መጠመቅ
ሉቃስ 3፥21-22
አጥማቂው ዮሐንስ እስራኤላውያንን እግዚአብሔርን ደስ የሚያሰኝ ሕይወት እንዲኖሩ አበረታታቸው። ከዚህ የተነሳ ክፉ ስራቸውን ትተው ወደ እግዚአብሔር የተመለሱትን ብዙ ሰዎች በዮርዳኖስ ወንዝ አጠመቃቸው። በተጨማሪም እግዚአብሔር ተስፋ የሰጣቸው አዳኝም ከትንሽ ጊዜ በኋላ እንደሚመጣ ለሕዝቡ ይናገር ነበር።
አንድ ቀን ኢየሱስም መጥቶ በዮሐንስ በዮርዳኖስ ወንዝ ተጠመቀ። እንደተጠመቀም የእግዚአብሔር መንፈስ እርግብ መስሎ በእርሱ ላይ ወረደ። ወዲያውም “አንተ የምወድህ ልጄ ነህ! ሁልጊዜ ባንተ ደስ ይለኛል” የሚል የእግዚአብሔር ድምፅ ከሰማይ ተሰማ።
The Baptism of Jesus
Luke 3:21-22
John the Baptizer encouraged the Israelites to live as God wanted them to live. Many people listened to his message, stopped doing evil and turned to God. He baptized them in the river Jordan. He also told the people that the Saviour that God had promised would come soon.
One day also Jesus was baptized by John in the river Jordan. As he was baptized, God’s Spirit came down upon him in the form of a dove. Immediately God’s voice was heard from heaven: “You are my dear son, you always bring me great joy.”

ኢየሱስ ሲጠመቅ፥ የእግዚአብሔር መንፈስ እርግብ በመምሰል በእርሱ ላይ ሲወርድ
ኢየሱስ በተጠመቀ ጊዜ የማን ድምፅ ተሰማ?
የእግዚአብሔር ድምፅ ተሰማ።
85. ኢየሱስ የሰይጣንን ሐሳብ ተቃወመ
ሉቃስ 4፥1-11
ኢየሱስ ከተጠመቀ በኋላ ለአርባ ቀኖች ብቻውን በምድረ በዳ ቆየ። በዚህ ጊዜ ምንም ምግብ አልበላም። በእነዚህም ቀኖች* ሰይጣን ኢየሱስን የእርሱን መጥፎ ሐሳብ እንዲቀበል ለማድረግ ሞከረ። ኢየሱስ ግን የሰይጣንን የተንኮል ምክር በፍፁም አልተቀበለም። የነገረውን መጥፎ ሐሳቦች የእግዚአብሔርን ቃል ተጠቅሞ ተቃወመው። ሰይጣንም ሙከራው እንዳልተሳካለት ባየ ጊዜ ኢየሱስን ትቶ ሄደ። ከዚህ በኋላ ኢየሱስ ስለ እግዚአብሔር ማስተማር እና ሰዎችን ከተለያዩ በሽታዎች መፈወስ ጀመረ። ያን ጊዜ ዕድሜው ሠላሳ ዓመት ያህል ነበር።
Jesus Resists Satan’s Suggestions
Luke 4:1-11
After Jesus was baptized, he was in the desert on his own for fourty days. During that time he didn’t eat anything. And Satan came and tried to make him accept his evil ideas. But Jesus rejected his tricky advice. He countered all his evil suggestions with the word of God. When Satan saw that he was not successful, he left Jesus and went away.
Afterwards Jesus started to teach about God and heal people from all sorts of diseases. He was about thirty years old at the time.

ሰይጣን ኢየሱስን የእርሱን መጥፎ ሐሳብ እንዲቀበል ለማድረግ ሲሞክር
ኢየሱስ የሰይጣንን ሐሳብ ሲሰማ ምን አደረገ?
የሰይጣንን ሐሳብ ተቃወመው።
86. ኢየሱስ እና ዓሣ አጥማጆቹ
ሉቃስ 5፥1-11
አንድ ቀን ኢየሱስ ዓሳ አጥማጆች ባሉበት ሐይቅ አጠገብ አስተማረ። ትምህርቱን ከጨረሰ በኋላ ዓሳ አጥማጆቹን ዓሣዎችን በመረባቸው እንዲይዙ ነገራቸው። እነርሱም ሌሊቱን ሙሉ ሞክረው ምንም ዓሳ መያዝ እንዳልቻሉ መለሱለት። ኢየሱስ ግን ስለተናገራቸው እንደገና ለመያዝ ሞከሩ።
በዚህ ጊዜ እጅግ ብዙ ዓሳዎች ያዙ። ያገኙትም ዓሳዎች ብዛት ሁለት ጀልባዎች ሙሉ ነበር። በዚህም ኢየሱስ የእግዚአብሔር ኃይል እንዳለው አወቁ። የእርሱም ተከታዮች ለመሆን እና ከእርሱ ለመማር ወሰኑ።
Jesus and the Fishermen
Luke 5:1-11
One day Jesus taught beside a lake where there were some fishermen. After he finished teaching, he told the fishermen to try catching some fish with their nets. They responded that they had already tried the whole night and had not succeeded. But because Jesus told them to, they tried again. And this time they caught so many fish that they were able to fill two boats. By this they realized that God’s power was with Jesus. And they decided to become his followers and learn from him.

ዓሣ አጥማጆቹ ኢየሱስ እንዳላቸው ዓሳዎችን ለመያዝ መረባቸውን ሲጥሉ
ዓሣ አጥማጆቹ በኢየሱስ ቃል ብዙ ዓሳ ሲያገኙ ምን አወቁ?
ኢየሱስ የእግዚአብሔር ኃይል እንዳለው አወቁ።
87. ኢየሱስ ከትኩሳት ፈወሰ
ሉቃስ 4፥38-41+ ማቴ 8፥14-17
አንድ ቀን ኢየሱስ የጴጥሮስን ቤተሰብ ጎበኘ። የጴጥሮስ አማት በከባድ ትኩሳት ታማ ተኝታ ነበር። እዚያ የነበሩ ሰዎች ኢየሱስን እንዲፈውሳት ለመኑት። ኢየሱስም ልመናቸውን ሰምቶ ትኩሳቱ እንዲለቃት አዘዘው። ወዲያውኑ ከበሽታዋ ስለተፈወሰች ተነስታ አስተናገደቻቸው። በዚያን ቀን ማታ ኢየሱስ ሌሎችም ብዙ በሽተኞችን ፈወሰ። እንዲሁም በሰይጣን መናፍስት የሚጨነቁትን ሰዎች ነፃ አወጣቸው። ክፉ መናፍስቱም ኢየሱስ የእግዚአብሔር ልጅ መሆኑን እየጮሁ በመናገር ከሰዎች ይወጡ ነበር።
Jesus Heals From Fever
Luke 4:38-41 + Matthew 8:14-17
One day Jesus visited Peter’s family. Peter’s mother-in-law had high fever and was quite sick. When the people asked Jesus to heal her, he commanded the fever to leave. And she got well immediately. She got up and served the guests.
That evening Jesus healed many other sick people too. Also people who were troubled by evil spirits were set free. These spirits came out of the people screaming that Jesus is the Son of God.

ኢየሱስ የጴጥሮስን አማት ሲፈውስ
ኢየሱስ በኃይሉ ምን አደረገ?
ኢየሱስ በሽተኞችን ፈወሰ፥ እንዲሁም በሰይጣን መናፍስት የተጨነቁትን ነፃ አወጣ።
88. ኢየሱስ የቆዳ በሽተኛ ፈወሰ
ሉቃስ 5፥12-16
ኢየሱስ በእስራኤል ሀገር ስለ እግዚአብሔር እያስተማረ እና የታመሙትን እየፈወሰ ዞረ። ብዙ ሰዎቹም ከኢየሱስ ጋር የነበረውን የእግዚአብሔር ኃይል ሲያዩ በጣም ተገረሙ። እርሱንም አንዳንዶች ሲቀበሉት፥ አንዳንዶች ደግም አልተቀበሉትም ነበር።
አንድ ቀንም በከባድ ቆዳ በሽታ የታመመ ሰው ኢየሱስን አየ። እርሱም “ከፈለግህ፥ ልትፈውሰኝ ትችላለህ” አለው። ኢየሱስም “አዎን፥ እንድትፈወስ እፈልጋለሁ” አለው። ወዲያውም ሰውየው ሙሉ በሙሉ ተፈወሰ። ይህንንም ብዙ ሰዎች ሲሰሙ እንዲፈውሳቸው ወደ ኢየሱስ ተሰበሰቡ። እርሱ ግን እንደልማዱ ከሰዎች ርቆ ለብቻው ይጸልይ ነበር።
Jesus Heals a Man with Leprosy
Luke 5:12-16
Jesus traveled through the country of Israel teaching about God and healing many from their diseases. Many people were amazed at the power of God that was with Jesus. Some people liked him while others rejected him.
One day a man who was very sick with leprosy saw Jesus and said, “If you want, you can heal me.” Jesus told him in response, “Yes, I want to,” and the man was completely healed at once. Many people gathered around Jesus to be healed when they heard this. But Jesus withdrew to a lonely place to pray, as he did regularly.

ኢየሱስ የቆዳ በሽታ ያለበትን ሰው ሲፈወስ
የቆዳ በሽታ ያለበትን ሰው ወዲያውኑ ማን ፈወሰው?
የፈወሰው ኢየሱስ ነው።
89. የኢየሱስ ስልጣን በኃጢአት እና በበሽታ ላይ
ሉቃስ 5፥17-26
አንድ ቀን ሰዎች ሽባ የሆነ ጓደኛቸውን ይዘው ወደ ኢየሱስ መጡ። እርሱ የሚያስተምርበት ቤት ግን በሕዝብ የተሞላ ስለነበር መግባት አልቻሉም። ስለዚህ ከላይ የቤቱን ጣራ ከፍተው ጓደኛቸውን በኢየሱስ ፊት አወረዱት። እርሱም እምነታቸውን አይቶ ሽባውን “ኃጢአትህን ይቅር ብዬኃለሁ” አለው። ምክንያቱም ኢየሱስ የእግዚአብሔር ልጅ ስለሆነ፥ ኃጢአትን ይቅር የማለት ሥልጣን አለው። ይህንንም እንዲያውቁ ሽባውን ሰው ኃጢአቱን ይቅር ካለው በኋላ በኃይሉ ፈወሰው። በዚያም የነበሩ ሰዎች የሽባውን መፈወስ ሲያዩ፥ በኢየሱስ ሥልጣን እና ኃይል ተደነቁ።
Jesus’ Power to Forgive and to Heal
Luke 5:17-26
One day some men took their paralyzed friend to Jesus. But when they arrived, they were not able to enter the house where Jesus was teaching. It was too full of people. Therefore the men opened the roof from the outside and lowered their friend in front of Jesus. When Jesus saw their faith, he said to the paralyzed man, “Your sins are forgiven!” Because Jesus is the Son of God, he has the power to forgive sins. To prove this, he then healed the man immediately. When the people there saw that the paralyzed man was healed, they were amazed about the authority and power that Jesus had.

ሰዎቹ ሽባ የሆነውን ጓደኛቸውን ጣራውን ከፍተው ሲያወርዱት
ኃጢአትን ይቅር የማለት ሥልጣን ያለው ማን ነው?
ኃጢአትን ይቅር የማለት ሥልጣን ያለው ኢየሱስ ነው።
90. ኢየሱስ እና ስግብግብ ግብር ሰብሳቢው
ሉቃስ 5፥27-32
የሮም መንግሥት ገንዘብ ሰብሳቢው ሌዊ ስግብግብ ሰው ነበር። ከሰዎች ከመጠን በላይ ገንዘብ ይወስድ ነበር። አንድ ቀን ኢየሱስ ሌዊ የግብር ገንዘብ ሲሰበስብ አይቶ “ተከተለኝ” አለው። ሌዊም ወዲያውኑ ከኢየሱስ ጋር ሄደ። በሌዊም ቤት አብረው ምግብ በሉ። በዚያ ሌሎች ብዙ ክፉ ሰዎች እና ኃጢአተኞች ነበሩ። የእግዚአብሔር ሕግ አስተማሪዎች ይህንን ባዩ ጊዜ “ኢየሱስ እና ተከታዮቹ ለምን ከኃጢአተኞች ጋር ይበላሉ?” ብለው ተቆጡ። ኢየሱስም “ኃጢአተኞችን ለማዳን መጥቻለሁ። ለዚህ ነው አብሬአቸው የምሆነው” አላቸው።
ኢየሱስ በምሕረት የተሞላ አዳኝ ነው።
Jesus and the Greedy Tax Collector
Luke 5:27-32
Levi was a tax collector for the Roman king. He was a greedy man who regularly took more money from people than he was supposed to do. One day Jesus saw him as he was collecting tax and said to him, “Follow me!” And he went with Jesus immediately. When they ate together at Levi’s house, there were also many other evil people and sinners there. When the teachers of God’s law saw this, they became angry and said, “Why do Jesus and the disciples eat with sinners?” Jesus answered them, “I have come to save sinners. That is why I have fellowship with them.”
Jesus, our Saviour, is full of mercy.

ኢየሱስ ከኃጢአተኞች እና ከክፉ ሰዎች ጋር ሲበላ
ኢየሱስ ኃጢአተኞችን እና ክፉ ሰዎችን ይቅር ማለት ይወዳል?
አዎን፥ ይቅር ማለት ይወዳል።
91. የተባረከ ማን ነው?
ሉቃስ 6፥12-42
አንድ ጊዜ ኢየሱስ በተራራ ላይ ሆኖ ሌሊቱን ሙሉ ጸለየ። በማለዳም ከተከታዮቹ 12 ሐዋርያትን መረጠ። ከተራራው ከወረዱ በኋላ እዚያ ተሰብሰበው ለነበሩት ሰዎች ማን የተባረከ እንደሚሆን አስተማራቸው። እርሱም “የሚወድዱንን ሰዎች መወደድ ቀላል ነው። የተባረካችሁ እንድትሆኑ ግን የሚወዷችሁን ብቻ ሳይሆን፥ የሚጠሏችሁንም ሁሉ ውደዱ። ለሚጠሏችሁ መልካም ካደረጋቸሁ፥ የእግዚአብሔር ልጆች መሆናችሁ በዚህ ይታወቃልና። ለጠላቶቻቸሁ ጸልዩላቸው፥ ደግሞም ባርኳቸው። ለሰዎች የምታደርጉትን ሁሉ በመልካም ሐሳብ አድርጉ። በእናንተም ላይ እንዳይፈረድባችሁ፥ በሰዎች ላይ አትፍረዱ!” አላቸው።
Who Is Blessed?
Luke 6:12-42
One time Jesus prayed all night long on a mountain. After that he chose 12 of his followers to be apostles. When he came down the mountain, he also explained to the crowd that was gathered there how they could be blessed.
Jesus taught: “It is easy to love someone who loves you. In order to be blessed, do not only love people who love you, but also all those who hate you. If you do good to those who hate you, it will show that you are children of God. Pray for your enemies and bless them! Do everything that you do to others with good intentions. Don’t judge others, so that you will not be judged.”

ኢየሱስ መልካም ማድረግ እና ሰዎችን ሁሉ ስለ መውደድ ሲያስተምር
መልካም ማድረግ ያለብን ለማን ነው?
ለሚወዱን ብቻ ሳይሆን፥ ለሚጠሉንም መልካም ማድረግ አለብን።
92. ትክክለኛ ጸሎት
ማቴዎስ 6፥5-15
ኢየሱስ ስለ ጸሎት ለሕዝቡ እንዲህ ሲል አስተማረ፡-
ስትጸልዩ በሰዎች ለመታየት ፈልጋችሁ አትጸልዩ! ትዕቢተኛ ሰዎች ሁሉም ሊያያቸው በሚችል ቦታ ሆነው መጸለይ ይወዳሉ። ይህንን የሚያደርጉት ከሰዎች ክብር ማግኘት ስለሚፈልጉ ነው። እግዚአብሔር ግን እንደዚህ ዐይነት ጸሎትን አይወድም። ስለዚህ ስትጸልዩ ወደ ቤታቸሁ ገብታቸሁ በእግዚአብሔር ፊት በትሑት ልብ ጸልዩ! ከሰዎች ለጸሎታቸሁ ምንም ክበር አትጠብቁ! በተጨማሪም፥ በምትጸልዩበት ጊዜ ቃላትን ብዙ አትደጋግሙ! ምክንያቱም በሰማይ የሚኖር አባታችሁ ገና ሳትጠይቁት የሚያስፈልጋችሁን ሁሉ ያውቃል።
The Right Prayer
Matthew 6:5-15
Jesus taught about praying:
“When you pray, do not pray in order to be seen by others. Proud people love to pray at places where everyone can see them. They do that, so that others think highly of them. But God does not reward such prayers. Therefore, go inside your house and pray to God with a humble attitude. Don’t expect to receive honour from other people for your prayers! Also, much repetition is not necessary when you pray, since your heavenly Father knows what you need even before you ask him.”

ብቻውን በእግዚአብሔር ፊት የሚጸልይ ሰው እና ከሰዎች ክብር ለማግኘት የሚጸልይ ሰው
ወደ እግዚአብሔር ስንጸልይ እንዴት መጸለይ አለብን?
ራሳችን ዝቅ አደርገን በትሕትና፥ ያለ ትዕቢት መጸለይ አለብን።
93. በዓለት ላይ ቤት መስራት
ሉቃስ 6፥46-49
ኢየሱስ ስለ መንፈሳዊ የሕይወት መሰረት በምሳሌ ተናገረ። እርሱም
“ቤታቸውን በጠንካራ ዓለት ላይ የሚሰሩ ሰዎች ጠቢባን ናቸው። ምክንያቱም በዓለት ላይ ስለተሰራ፥ ምንም ዐይነት ችግር ቢመጣ አይወድቅምና። በአሸዋ ላይ ቤት የሚሰሩ ሰዎች ደግሞ ሰነፎች ናቸው። ምክንያቱም ጎርፍ እና ነፋስ ሲመጣ፥ የተሰራው ቤት ይፈርሳልና። ስለዚህ እኔ የማስተምረውን መንፈሳዊ ትምህርት ሰምቶ የሚታዘዝ ሰው ቤቱን በዓለት ላይ እንደሚሰራ ዐይነት ጠቢብ ሰው ነው። ይህ ሰው መከራ እና ችግር ቢያጋጥመው ቃሌ የሕይወቱ መሰረት ስለሆነ፥ በቀላሉ አይወድቅም። እኔ የምለውን ሰምቶ የማያደርግ ሰው ግን ቤቱን በአሸዋ ላይ እንደሚሰራ ዐይነት ሰነፍ ሰው ይመስላል። ይህ ሰው መከራ እና ችግር ቢያጋጥመው በቀላሉ ይወድቃል” ሲል አስተማረ።
The House Built on the Rock
Luke 6:46-49
Jesus used an example when he taught about the spiritual foundation of life. He said:
“People who build their house on a rock are wise people. When any kind of trouble comes, the house stands firm, because it is built on a rock. People who build their house on sand, on the other hand, are unwise. For when a flood or a storm comes the house built on sand quickly collapses. People who do what I teach are wise like people who build their house on a rock. When they suffer or get in trouble, they will stand firm, because my word is the foundation of their life. But people who understand what I say but do not live accordingly, are unwise like people who build their house on sand. When such people suffer or troubles come, they are not able to stand strong.”

ጎርፍ ሲመጣባቸው የፈረሰው በአሸዋ ላይ የተሰራው ቤት እና ያልፈረሰው በዓለት ላይ የተሰራው ቤት
በጠንካራ መሰረት ላይ ቤት እንደሚሰሩ ዐይነት የሆኑ ጠቢባን ሰዎች እነማን ናቸው?
የኢየሱስን ትምህርት ሰምተው የሚታዘዙ ሰዎች ናቸው።
94. የሮማዊው መሪ እምነት
ሉቃስ 7፥1-10
አንድ ጊዜ የአንድ ሮማዊ መሪ ሰራተኛ በጣም ታመመ። ሰዎችንም ወደ ኢየሱስ እንዲፈውሰው ለመለመን ላከ። መሪው እስራኤላዊ ባይሆንም፥ ለእነርሱ ብዙ መልካም ነገሮችን አድርጎ ነበር። ኢየሱስም ተነስቶ ወደ ቤቱ ሲቀርብ፥ መሪው ወዳጆቹን ልኮ “ወደ ቤቴ ልተገባ እና በአካል ልገናኝኽ አይገባኝም። እኔ ለሰራተኞቼ ትእዛዝ ስሰጣቸው፥ ያልኳቸውን ሁሉ ያደርጋሉ። ስለዚህ አንተም ቃል ብቻ ከተናገርክ፥ ሰራተኛዬ ይድናል” ብሎ ለመነው። ኢየሱስም በመሪው እምነት ተገረመ። ወደ በሽተኛውም ቤት ሳይገባ ቃል ብቻ በመናገር ፈወሰው።
The Faith of a Roman Leader
Luke 7:1-10
One day the servant of a Roman leader became very sick. So he sent people to ask Jesus for his servant to be healed. Although the leader was not from the people of Israel, he did many good things for them. When Jesus was on his way to his house, the leader sent his friends with this message, “I am not worthy that you come to my house to meet me. I can give commands to my workers, and they do everything I say. In the same way, if you command it, my servant will be healed.” Jesus was amazed by the leader’s faith. And without entering his house, he healed the sick person by just speaking a word.

ሰዎች ኢየሱስ የሮማዊውን ሰራተኛ እንዲፈውስለት ሲለምኑት
ኢየሱስ የሮማዊውን ንግግር ሰምቶ ለምን ተገረመ?
ኢየሱስ በእምነቱ ተገረመ።
95. ኢየሱስ ወጣት* ከሞት አስነሳ
ሉቃስ 7፥11-17
ኢየሱስ ከተከታዮቹ ጋር ወደ አንድ ከተማ ሄደ። ወደ ከተማዋ በር ሲደርሱ፥ ሰዎች የሞተ ሰው ተሸክመው ወደ መቃብር ሲሄዱ አየ። እርሱም የአንዲት ባሏ የሞተባት ሴት ብቸኛ ልጅ ነበር። ኢየሱስም አዘነላት እና “አይዞሽ፥ አታልቅሺ!” አላት። ከዚያም ወደ ሬሳው ቀርቦ “አንተ ወጣት፥ ተነሳ!” አለው። ወዲያውኑ ከሞት ተነሳ። ተቀምጦም መናገር ጀመረ። በዚህ መንገድ ይህች እናት ብቸኛ ልጇን እንደገና አገኘች። ሕዝቡም ይህንን ባዩ ጊዜ እግዚአብሔርን አመሰገኑ።
Jesus Raises a Young Man From Death
Luke 7:11-17
Afterwards Jesus went together with his followers to another town. When he arrived at the town gate, he noticed how people carried a dead person to the grave. The dead young man was the only son of a widow. Jesus felt sorry for her and said, “Take heart, don’t cry!” Then he drew close to the dead body and said, “Young man, get up!” Immediately he came back to life, sat up and started to speak. This way the widow received her only son back. When the people saw what had happened, they praised God.

ኢየሱስ ወጣት ከሞት ሲያስነሳ
ሰዎቹ እግዚአብሔርን ያመሰገኑት ለምንድን ነው?
እግዚአብሔርን ያመሰገኑት ኢየሱስ የሞተውን ወጣት ስላስነሳው ነው።
96. ኢየሱስ ኃይለኛውን ነፋስ አቆመ
ሉቃስ 8፥22-25
አንድ ጊዜ ኢየሱስ እና ተከታዮቹ በጀልባ ሐይቅን ሲሻገሩ ኃይለኛ ነፋስ ተነሳ። በነፋሱ ምክንያት ውሃ ወደ ጀልባዋ እየገባ ይሞላት ስለነበር፥ ተከታዮቹ በጣም ፈሩ። በዚያን ጊዜ ግን ኢየሱስ በጀልባው ውስጥ ተኝቶ ነበር። ስለዚህም ኢየሱስን ከእንቅልፍ ቀስቅሰው “ኢየሱስ! ተነሳ፥ እርዳን!” ብለው ጮኹ። እርሱም ተነስቶ ነፋሱን እና የሚናወጠውን ውሃ ጸጥ እንዲሉ አዘዛቸው። ወዲያውም ኃይለኛው ነፋስ እና የሚናወጠው ውሃም ጸጥ አሉ። ተከታዮቹም ተደነቀው “በነፋስ እና በውሃ ላይ እንደዚህ ዐይነት ሥልጣን ያለው እርሱ ማን ነው?” ተባባሉ።
Jesus Stills the Storm
Luke 8:22-25
One time Jesus and his followers were crossing a lake by boat when a storm arose. The boat started filling with water and the disciples were very scared. But Jesus was still sleeping in the boat. So they woke him up shouting, “Jesus, get up! Help us!” Jesus got up and commanded the storm and the raging water to be quiet. Immediately the storm stopped, and the lake became calm. The disciples were astonished and said to each other, “Who is this man who even has authority over wind and water?”

ኢየሱስ ነፋሱን እና ውሃውን ጸጥ እንዲሉ ሲያዝ
የኢየሱስ ተከታዮች ለምን ተደነቁ?
ኃይለኛው ነፋስ እና የሚናወጠው ውሃ ለኢየሱስ ስለታዘዙ ነው።
97. ከሰይጣን መናፍስት ነፃ የወጣው ሰው
ሉቃስ 8፥26-39
ኢየሱስ እና ተከታዮቹ ከሐይቁ ማዶ ሲደርሱ፥ አንድ ብዙ የሰይጣን መናፍስት ያለበት ሰው መጣ። ሰውየውም በሰይጣን መናፍስቱ እጅግ እየተሰቃየ በመቃብር ቦታ ይኖር ነበር። እርሱም የሚታሰርበትን ሰንሰለት ስለሚሰባብር፥ ማንም ሊይዘው አይችልም ነበር። ኢየሱስ ግን መናፍስቱን ከሰውየው ወጥተው እንዲሄዱ አዘዛቸው። ወዲያውም ወጥተው በቅርብ ወደ ነበሩት ዐሣማዎች ውስጥ ገቡ። ዐሣማዎቹም ወደ ሐይቁ ሮጠው ሰመጡ። ሰውየውም ከሰይጣን መናፍስቱ ነፃ ስለወጣ፥ ኢየሱስን በጣም አመሰገነ። እግዚአብሔርም ያደረገለትን በከተማው ሁሉ እየዞረ ተናገረ።
Freed from Many Evil Spirits
Luke 8:26-39
When Jesus and his followers arrived on the other side of the lake, a man possessed by many evil spirits came towards him. He was very troubled by these spirits and was living in a graveyard. Nobody was able to keep him tied up, because he would simply break the chains he was tied up with.
But Jesus commanded the spirits to leave the man. So all of them left him immediately and moved into a herd of pigs nearby. As a result, the pigs ran into the lake and drowned. The man was really grateful that Jesus had set him free from the evil spirits. And he told everyone in his town what God had done for him.

ኢየሱስ የሰይጣን መናፍስቱን ከሰውየው ወጥተው እንዲሄዱ ሲያዛቸው
በሰይጣን መናፍስት የተሰቃየውን ሰው ማን ነፃ አወጣው?
ኢየሱስ ነፃ አወጣው።
የሰይጣን መናፍስቱ ከሰውየው ወጥተው ለምን ሄዱ?
ኢየሱስ ስላዘዛቸው ወጥተው ሄዱ።
98. ከሞት የተነሳችዋ ልጅ
ሉቃስ 8፥40-56
አንድ ቀን አንድ መሪ ብቸኛ ልጁ ታመመችበት። ወደ ኢየሱስም መጥቶ ልጁን እንዲፈውስለት ለመነው። ኢየሱስም አብሮት ወደ ቤቱ በመሄድ ላይ እያለ ሰዎች መጥተው ልጁ እንደሞተች ነገሩት። ኢየሱስ ግን ሰዎቹ ያሉትን ሰምቶ መሪውን “በእኔ ታመን እንጂ አትፍራ! ልጅህ ትድናለች” አለው። በመሪው ቤት ሲደርሱ፥ ኢየሱስ የሚያልቅሱትን ሰዎች ዝም እንዲሉ ነገራቸው። ከዚያም ከወላጆቿ እና ከሦስት ተከታዮቹ ጋር ወደ ቤት ውስጥ ገብቶ “አንቺ ልጅ፥ ተነሺ!” አላት። እርሷም ወዲያው ከሞት ተነሳች። ኢየሱስም ለወላጆቿ ምግብ እንዲሰጧት ነገራቸው።
A Dead Girl Comes Back to Life
Luke 8:40-56
One day a leader came to Jesus and asked him to heal his sick daughter. She was his only child. While Jesus was going with him to his house some people came and told him that his child had just died. Jesus heard it and said to him, “Don’t be afraid, but trust in me. Your daughter will be fine.” When they arrived at the leader’s house, Jesus told the people who were wailing there to be quiet. Then he went inside with the parents of the girl and three of his followers. There he said to her, “Wake up, girl!” And she immediately came back to life. Then Jesus told her parents to give her something to eat.

ኢየሱስ የሞተችውን ልጅ ከሞት ሲያስነሳት
ኢየሱስ ማንን ከሞት አስነሳ?
የመሪውን ልጅ ከሞት አስነሳ።
99. ኢየሱስ ሐዋሪያቱን ላከ
ሉቃስ 9፥1-6
አንድ ቀን ኢየሱስ ለሐዋሪያቱ ኃይል ሰጥቶ “በዚህ አካባቢ ባሉ ከተሞች ሄዳችሁ ስለ እግዚአብሔር መንግሥት ለሕዝቡ ተናገሩ። በሽተኞችን ፈውሱ፥ ደግሞም በሰይጣን መናፍስት የሚጨነቁትን ሰዎች ነጻ አውጡ!” ብሎ ላካቸው። በተጨማሪም በዚህ ጊዜ “ለጉዞአችሁ የሚሆን እንደ ቦርሳ፥ ዳቦ፥ ገንዘብ ያሉ ነገሮችን አትያዙ!” አላቸው። ይህንን ያላቸው እግዚአብሔር በሄዱበት ቦታ የሚያስፈለጋቸውን ሁሉ ስለሚሰጣቸው ነው።
Jesus Sends His Apostles
Luke 9:1-6
One day Jesus gave power to his apostles and said, “Go to the towns in this area and tell the people about the Kingdom of God! Heal the sick and set people free from the evil spirits which bother them.”
At the same time he also told them, “Don’t take anything with you on your journey like a travel bag, bread or money.” He said this, because God would provide what they needed in every place they visited.

ኢየሱስ ለሐዋሪያቱ ኃይል ሰጥቶ ወደ ከተሞች ሲልካቸው
ኢየሱስ ሐዋሪያቱን ምን እንዲያደርጉ ላካቸው?
የላካቸው ስለ እግዚአብሔር መንግሥት እንዲናገሩ እና በሽተኞችን እንዲፈውሱ ነው።
100. ኢየሱስ በተአምር 5000 ሰዎች መገበ
ሉቃስ 9፥10-17 + ዮሐንስ 6፥1-14
የኢየሱስ ሐዋሪያት ወደ እርሱ ተመልሰው በከተሞች ያደረጉትን ተአምራት ሁሉ ነገሩት። ከዚያም ለብቻቸው ለመሆን ከሰዎች ራቅ አሉ። ብዙ ሕዝብ ግን ኢየሱስን ፈልገው ተከትለዋቸው ወዳሉበት ቦታ መጡ። ኢየሱስም ሕዝቡን ስለ እግዚአብሔር መንግሥት አስተማረ፥ በሽተኞችንም ፈወሰ። በመሸም ጊዜ ምግብ እጅግ ብዙ ለሆነው ሕዝብ ከየት እንደሚያገኙ ተወያዩ። ኢየሱስ ግን አንድ ልጅ ያመጣውን ሁለት ዓሣ እና አምስት እንጀራ አንስቶ እግዚአብሔርን አመሰገነ። ከዚያም ምግቡን ለሕዝቡ እንዲያከፋፍሉ ለተከታዮቹ ሰጣቸው። እግዚአብሔር ትንሹን ምግብ ስለባረከው፥ ከ5000 በላይ ለሆኑ ሰዎች የሚበቃ ሆነ። ሰዎችም በልተው ከጠገቡ በኋላ፥ 12 መሶብ ሙሉ እንጀራ ተረፈ።
Jesus Miraculously Feeds 5000
Luke 9:10-17 + John 6:1-14
The apostles returned to Jesus and told him about all the miracles they had done in the towns. Together they went away from the crowds to be by themselves. But many people searched for Jesus, and followed them to the place they had gone. So Jesus taught the people about the Kingdom of God and healed many sick people.
When it got dark, they discussed how they could get food for such a big crowd. But Jesus took the two fish and five small bread loaves that a boy had brought with him and thanked God. Then he gave it to his followers to distribute it to the people. Because God blessed this small amount of food, it was enough for more than 5000 people. When all were satisfied, there were even 12 baskets full of bread left over.

ኢየሱስ ትንሹን ዓሳ እና እንጀራ እንዲበዛ ሲባርክ
ሁለት ዓሳ እና አምስት እንጀራ ለ5000 ሰዎች እንዴት ሊበቃ ቻለ?
እግዚአብሔር ትንሹን ምግብ ስለባረከው ነው።
101. ኢየሱስ በውሃ ላይ ተራመደ
ማቴዎስ 14፥22-33
ቀጥሎም ኢየሱስ ተከታዮቹ በጀልባ ሐይቁን እንዲሻገሩ ነገራቸው። እርሱ ግን ብቻውን ሊጸልይ ወደ አንድ ተራራ ወጥቶ እዚያው ለረጅም ሰዓት ቆየ። ተከታዮቹ በጀልባ ሲጓዙ፥ ከባድ ነፋስ ከፊታቸው ተነስቶ ያስጨንቃቸው ጀመር። ሌሊቱ ሊነጋ ትንሽ ሲቀረው፥ ኢየሱስ በውሃው ላይ እየተራመደ ወደ እነርሱ መጣ። እነርሱ ግን መንፈስ የሚያዩ ስለመሰላቸው፥ በፍርሀት ተንቀጥቅጠው ጮኹ። ኢየሱስም “እኔ ነኝ! አትፍሩ!” ብሎ አበረታቸው። ጴጥሮስም ኢየሱስን “በውሃው ላይ ወደ አንተ ልምጣ?” ብሎ ሲጠይቀው፥ “ና!” አለው። እርሱም ከጀልባዋ ወርዶ ትንሽ በውሃ ላይ ከተራመደ በኋላ፥ ነፋሱን እና ማዕበሉን ባየ ጊዜ ግን ፈራ። መስመጥም ስለጀመረ፥ ኢየሱስ እንዲያድነው ጮኸ። ወዲያውም ኢየሱስ እጁን ይዞ አወጣውና “ለምን በእኔ መታመን አቃተህ? ታመን እንጂ አትጠራጠር!” አለው። ከጴጥሮስም ጋር ወደ ጀልባዋ ገባ። ተከታዮቹም ይህንን ባዩ ጊዜ፥ ኢየሱስ የእግዚአብሔር ልጅ መሆኑን አውቀው ሰገዱለት።
Jesus Walks on Water
Matthew 14:22-33
Straight after, Jesus commanded his disciples to cross the lake by boat. Meanwhile, he went up a hill alone to pray and stayed there for a long time. While Jesus’ followers were in the boat, a strong wind arose and troubled them. Not long before dawn, Jesus came to them walking on the water. When the disciples saw him coming, they trembled and screamed with fear, because they thought they were seeing a ghost. But Jesus reassured them saying, “It’s me! Don’t be afraid.” Peter then asked Jesus, “Shall I come to you on the water?” and Jesus responded, “Come!” So Peter got out of the boat and started walking on the water. But when he looked at the waves and the storm, he became frightened and began to sink. He screamed for Jesus to save him. Immediately Jesus pulled him up and said, “Why do you trust in me so little? Don’t doubt!” Then they both got into the boat. When the disciples saw what happened, they knew that Jesus was the Son of God and worshipped him.

ኢየሱስ በውሃው ላይ እየተራመደ ሲሄድ
የነፋስን ማዕበል ከማየት እና ኢየሱስን ከማየት የትኛው ይሻላል?
ኢየሱስን ማየት እና በእርሱ መታመን ይሻላል።
102. ኢየሱስ ከሙሴ እና ከኤልያስ ጋር
ማቴዎስ 17፥1-8 + ሉቃስ 9፥28-36
አንድ ቀን ኢየሱስ ተከታዮቹ የሆኑትን ጴጥሮስ፥ ዮሐንስ እና ያዕቆብን ይዞ ወደ ተራራ ወጣ። ኢየሱስ በዚያ መጸለይ ሲጀምር፥ ፊቱ እና የለበሰውም ልብስ የሚያበራ ሆነ። ከብዙ ዘመናት በፊት የኖሩት ሙሴ እና ኤልያስ በተአምር ከኢየሱስ አጠገብ ታዩ። እግዚአብሔር በኢየሱስ እንዲሰራ ስላሰበው እቅድ አብረው ተነጋገሩ። ይህም እቅድ ኢየሱስ ስለ ሰው መዳን መከራ መቀበል፥ መሞት እና መነሳት እንዳለበት ነበር።
ከዚያም ደመና መጥቶ ሁሉንም ሸፈናቸው። ከደመና ውስጥ፡- “ኢየሱስ ልጄ ነው፥ እወደዋለው። እርሱን ስሙት!” የሚል የእግዚአብሔርን ድምፅ መጣ። ደመናው በጠፋ ጊዜ ከኢየሱስ እና ተከታዮቹ በስተቀር ማንም አልነበርም።
Jesus, Moses and Elijah
Matthew 17:1-8 + Luke 9:28-36
One day Jesus went up a mountain. He took Peter, John and James along. As Jesus started to pray there, his face and his clothes became very shiny. Then Moses and Elijah who had lived many generations before, miraculously appeared beside him. They talked with him about God’s plan. This plan was that Jesus had to suffer and die in order to save people. And he would rise from death again.
After this a cloud came and covered them all. They heard God’s voice from inside the cloud, “Jesus is my son, I love him! Listen to him!” When the cloud was gone, there was no one there except Jesus and his three followers.

ሙሴ እና ኤልያስ በተራራ ላይ ከኢየሱስ ጋር ሲነጋገሩ
ሙሴ እና ኤልያስ ከኢየሱስ ጋር ምን ተነጋገሩ?
ኢየሱስ ሰዎችን ለመዳን ስለሚሰራው ስራ ተነጋገሩ።
103. ደጉ ሳምራዊ
ሉቃስ 10፥29-37
አንድ ጊዜ ኢየሱስ ሰዎችን በትክክል የሚወድ ሰው ማን እንደሆነ እንዲህ ሲል በታሪክ አስተማረ፡-
አንድ ኢስራኤላዊ ከኢየሩሳሌም ወደ ኢያሪኮ ከተማ ተጓዘ። በመንገድ ላይ ዘራፊዎች መጡበት። በኃይል ደብድበው እና የነበረውን ዘርፈው ጥለውት ሄዱ። ከዚህም በኋላ አንድ ካህን በዚያ ሲያልፍ የተደበደበውን ሰው አየው። ሆኖም ግን ከሞት እንዲተርፍ ምንም ሳይረዳው ትቶት ሄደ። ቀጥሎም ሌላ የእግዚአብሔር አገልጋይ አየው። እርሱም ሳያዝንለት አልፎት ሄደ። ሁለቱ ሰዎች እስራኤላውያን ቢሆኑም ምንም አልረዱትም።
በመጨረሻ የሰማርያ ሀገር ሰው በዚያ መንገድ መጣ። ሰማርያውያን በእስራኤላውያን የተናቁ ነበሩ። ሆኖም ግን ይህ ሳምራዊ በዘራፊዎች የተደበደውን ሰው ሲያይ እጅግ አዘነለት። ወዲያውኑ የህክምና እርዳታ አደረገለት። በራሱም አህያ ላይ አስቀምጦ ሰው ሊረዳው እና ሊንከባከበው ወደሚችል ቦታ ወሰደው። በተጨማሪም ለሚያስፈልገው የምግብ እና የመድሃኒትም ዋጋ ከፍሎለት ሄደ።
The Good Samaritan
Luke 10:29-37
One time Jesus taught the people what it means to really love other people by telling this story:
An Israelite travelled from Jerusalem to the city of Jericho. Robbers attacked and robbed him on the way. After beating him up, they left him severely injured. A short while later, a priest saw him as he passed by. But he didn’t do anything to save his life. Next, another servant of God came by. He didn’t have pity on the injured man either. Both men belonged to the injured man’s own people. But they didn’t stop to help him.
In the end, a man from another area – from Samaria – arrived. Israelites despised Samaritans. Even so, this Samaritan felt sorry for the injured man from Israel. He gave him first aid, put him on his donkey and took him to a safe place where he was able to receive further care. In addition the Samaritan paid for food and medication for the injured man before he continued his journey.

የሰማርያ ሰው ለተደበደው ሰው በማዘን ከሞት እንዲተርፍ ሲረዳው
ኢየሱስ እንደ ሰማርያ ሰው ለእኛ ብዙ ደግነት እንዳደረገ፥ እኛስ ለሰዎች ምን ማድረግ አለብን?
እኛም ለሰዎች ሁሉ ደግነትን ማድረግ አለብን።


በታሪክ 78-103 ፈልግ፡