tig-66
128-150 የኢየሱስ ሞት፥ ትንሳኤ እና ሐዋሪያቱ
Jesus’ Death, Resurrection and the Apostles

ኣብ ታሪኽ 128-150 ድለዩ፡
128. የፋሲካ እራት
ሉቃስ 22፥7-30
ኢየሱስ ጴጥሮስን እና ዮሐንስን የእስራኤላውያንን የፋሲካ በዓል ለማክበር ቦታ እንዲያዘጋጁ ላካቸው። እነርሱም የት ቦታ ማድርግ እንደሚፈልግ ሲጠይቁት፥ እርሱ “ኢየሩሳሌም በገባችሁ ጊዜ፥ ውሃ የተሸከመ ሰው ታገኛላችሁ። ወደ ሚገባበት ቤት ተከትላችሁ ለፋሲካ እራታችን የሚመች ክፍል ጠይቁት!” አላቸው። እነርሱም ሄደው ሁሉን ነገር ኢየሱስ እንደተናገረው ሆኖ አገኙ። የቤቱም ባለቤት ደህና ክፍል አሳያቸው። እነርሱም በዚያ ለበዓሉ ዝግጅት አደረጉ።
በኋላም ኢየሱስ እና አሥራ ሁለቱ ሐዋርያት በክፍሉ የፋሲካን እራት አብረው በሉ። በዚያም በቅርብ ጊዜ እንደሚሞት ነገራቸው። እርሱም እንደ ፋሲካው ዳቦ እንደሚቆረስ እና ደሙም እንደ ወይን እንደሚፈስ በምሳሌ ገለጸላቸው። እስራኤላውያንንም የፋሲካው የበግ ደም በግብጽ ከሞት እንዳዳናቸው፥ የእርሱም ሞት ሰዎችን ከዘለአለም ሞት የሚያድን መሆኑን ኢየሱስ ያውቅ ነበር።
The Last Supper 
Luke 22:7-30
Jesus told Peter and John to prepare for the celebration of the Israelite Passover feast. After they asked where he wanted to celebrate, he explained, “When you enter Jerusalem, you will meet a man who is carrying water. Follow him and ask him about a room we can use to celebrate the Passover meal.” They went and found everything just like Jesus had said. The owner of the house showed them a suitable room. And they prepared for the feast there.
Later Jesus and his 12 disciples together ate the Passover meal in that room. He told them again that he would die soon. He explained that he would be broken like the bread, and his blood would be poured out like the wine of the Passover supper. In Egypt the blood of the Passover lamb had saved the Israelites from death. Jesus was aware that he was the Lamb of God in a similar way. By his death he saves people from eternal punishment.

ኢየሱስ ከመሞቱ በፊት ከሐዋርያቱ ጋር ለመጨረሻ ጊዜ አብረው ሲበሉ
እኛንም እግዚአብሔር በሰማይ ወዳዘጋጅው ግብዣ ጋብዞናል? 
አዎን፥ ጋብዞናል።
129. ኢየሱስ የሐዋርያቱን እግር አጠበ 
ዮሐንስ 13፥1-17
ኢየሱስ ከሐዋርያቱ ጋር በፋሲካ እራት ጊዜ እግራቸውን ለማጠብ ተነሣ። ጴጥሮስ ግን ጌታ ኢየሱስ ለምን ይህን ማድረግ እንደፈለገ አልገባውም ነበር። ስለዚህ ኢየሱስን
“አንተ እግሬን አታጥበኝም” አለው። ኢየሱስም እግሩን በእርሱ መታጠቡ አስፈላጊ መሆኑን አስረዳው። ጴጥሮስም በዚህ ከተስማማ በኋላ፥ ኢየሱስ እግሩን አጠበው። ጌታችን ኢየሱስ ታላቅ አስተማሪ እና አምላክ ቢሆንም፥ ተከታዮቹን በትሕትና ዝቅ ብሎ መልካም በማድረግ አገለገላቸው። እርሱ ምሳሌ ሆኖ ለእነርሱ እንዳደረገ እነርሱም ደግሞ እርስ በርሳቸው እንደዚሁ እንዲያደርጉ ነገራቸው።
Jesus Washes the Apostles’ Feet 
John 13:1-17
At the time of the Passover celebration, Jesus got up to wash his apostles’ feet. But Peter didn’t understand why Jesus wanted to do this. Therefore he said to him, “You will certainly not wash my feet!” So Jesus helped him to understand that this was very important. Then Peter agreed and Jesus washed his feet.
Jesus, the LORD Almighty, was a great teacher and yet he served his followers humbly like a servant by doing them good. As followers of Jesus, we should serve each other humbly just like he did. Let us follow his example.

ጌታ ኢየሱስ የሐዋርያቱን እግር ሲያጥብ
ኢየሱስ እርስ በእርሳችን እንዴት እንድናገለግል ይፈልጋል? 
ኢየሱስ ራሳችንን ዝቅ አድርገን በትሕትና እንድናገለግል ይፈልጋል።
130. መልካም ፍሬ ማፍራት
ዮሐንስ 15፥1-12
ኢየሱስ ለተከታዮቹ “እኔ እንደ ወይን ተክል ነኝ፥ እናንተ ደግሞ እንደ ቅርንጫፎቼ ናችሁ። ከእኔ ከተለያችሁ ምንም ማድረግ አትችሉም” አለ። ስለዚህ ከእርሱ ጋር ከሆነን እንደ ሰላም፥ ደስታ፥ ፍቅር፥ ታማኝነት፥ ትዕግሥት ዐይነት መልካም ፍሬ እናፈራለን። እግዚአብሔርም እኛን እንደ ወይን ቅርንጫፍ ብዙ መልካም ፍሬ እንድናፈራ ይንከባከበናል።
ኢየሱስ በተጨማሪም “እኔ እንደወደድኳችሁ፥ እናንተም እርስ በርሳችሁ ተዋደዱ!” ብሎ ተከታዮቹን አዘዛቸው።
ኢየሱስን መውደድ ማለት የተናገረውን ቃል ማድርግ ነው።
Bearing Good Fruit
John 15:1-12
Jesus said to his followers: “I am like a grape vine and you are like my branches. If you depart from me, you can’t do anything.” When we are connected to Jesus, we will bear good fruit like peace, joy, love, faithfulness and patience. God cares for us like someone cares for a branch of a plant called grape vine. He does that so that we will bear a lot of good fruit.
Jesus also commanded his followers: “You must love each other as I have loved you!”
To love Jesus means to obey his words.

አትክልተኛው ፍሬ የማያፈራውን ቅርንጫፍ ሲቆርጥ
መልካም ፍሬ ማፍራት የምንችለው እንዴት ነው?
ኢየሱስ የተናገረንን በማድርግ እና ከእርሱ ጋር በመኖር ነው።
131. ኢየሱስ ከመያዙ በፊት ጸለየ
ሉቃስ 22፥39-53
ኢየሱስ ከፋሲካ እራት በኋላ ኢየሩሳሌም ከተማ አጠገብ ወዳለው ደብረ ዘይት ወደ ተባለ ተራራ ወጣ። እዚያም ሐዋርያቱን ወደ ፈተና እንዳይገቡ እንዲፀልዩ ነገራቸው። እርሱም በቅርቡ የሚደርስበትን መከራ ስላወቀ በጣም ፈራ። ተንበርክኮ እንዲህም ሲል ጸለየ፡- “አባቴ፥ ሊመጣብኝ ወዳለ መከራ ውስጥ እንዳልገባ እባክህ ጠብቀኝ። ነገር ግን እኔ የምፈልገውን* ሳይሆን፥ ያንተ ፈቃድ እንዲሆን እፈልጋለሁ” አለ። የዚያን ጊዜ የእግዚአብሔር መልአክ መጥቶ አበረታው። ኢየሱስ ከጸለየ በኋላ ወደ ሐዋርያቱ መጣ። እነርሱ ግን መጸለይ ቢፈልጉም፥ ደክሟቸው ስለነበር ተኝተው አገኛቸው። ስለዚህ ኢየሱስ በዚህ በመከራው ሰዓት ብቻውን ነበር።
ብዙም ሳይቆይ ከሐዋርያቱ አንዱ ይሁዳ የተባለው ሰው፥ ኢየሱስን መያዝ ለሚፈልጉ ሰዎች መንገድ እየመራቸው መጣ። እነርሱም ወዲያውኑ ይዘውት ወደ ካህናት አለቃ ቤት ወሰዱት።
Jesus Prays Before His Arrest
Luke 22:39-53
After the Passover meal, Jesus went to the Mount of Olives just outside the city of Jerusalem. There he told his disciples to pray so that they would not sin when tempted. Jesus became very afraid because he was aware of the suffering that was just ahead of him. He knelt down and prayed, “Father, please protect me from the suffering that is about to come upon me. Yet, not what I want, but what you want should happen!” Then an angel came and made him strong. After this prayer he returned to his disciples. Even though they wanted to pray, they had fallen asleep. They were really tired. So Jesus was alone at this difficult time.
Soon afterwards, Judas – one of Jesus’ apostles – arrived. He was showing the people who wanted to seize Jesus where he was. They arrested him at once and took him to the house of Israel’s leading priest.

ኢየሱስ ከመሞቱ በፊት በጣም ፈርቶ ሲጸለይ እና ሐዋርያቱ ሲተኙ
ኢየሱስ በመከራው ሰዓት እንዴት ብሎ ጸለየ?
እግዚአብሔር ፈቃድ እንዲሆን ጸለየ።
132. ጴጥሮስ ፈርቶ ኢየሱስን ካደ
ሉቃስ 22፥54-62
ጴጥሮስ ኢየሱስን ለፍርድ ይዘውት ሲሄዱ ከሩቅ ሆኖ ተከተለው። እርሱም ኢየሱስ ወደ ገባበት ግቢ ገብቶ እሳት ይሞቁ ከነበሩ ሰዎች ጋር ተቀመጠ። ከጥቂት ጊዜ በኋላ አንድ ሰራተኛ አየችውና “ይህም ሰው ኢየሱስን ይከተል ነበር” አለች። ጴጥሮስም ስለፈራ “ትክክል አይደለም፥ እኔ አላውቀውም” ብሎ መለሰ። ደግሞም ሌሎች ሁለት ሰዎች ተራ በተራ “አንተም ከእርሱ ጋር ነበርህ” አሉት። ጴጥሮስ ግን ለሁለቱም “እኔ ይህንን የምትሉትን ሰው አላውቀውም” ብሎ ለሦስተኛ ጊዜ ሲክድ ዶሮ ጮኸ። ወዲያውም ኢየሱስ ጴጥሮስን ተመለከተ። ጴጥሮስም አስቀድሞ “ዶሮ ሳይጮኽ ሦስት ጊዜ ትክደኛለህ” ያለው ቃል ትዝ አለው። ኢየሱስንም ስለካደ ከግቢው ወጥቶ በጣም አለቀሰ።
Peter Denies Knowing Jesus
Luke 22:54-62
Peter followed the men who arrested Jesus from a distance. He entered the compound where they took Jesus, and he joined the people who were sitting around a fire to warm themselves. After a while, one of the workers looked at him and said, “This man was following Jesus.” And because Peter was afraid, he replied, “That’s not right. I don’t know him!” Later two others each commented, “You were also with him!” But Peter denied it both times with words like, “I don’t know who you are talking about!” After that a cockerel crowed and Jesus looked at Peter at once.
At this Peter remembered the words Jesus had said earlier, “Before the rooster crows, you will deny three times that you know me.” Then Peter left the compound and cried intensely, because he had denied Jesus.

ጴጥሮስ ስለፈራ “ኢየሱስን አላውቀውም” ብሎ ሲክደ
ጴጥሮስ ኢየሱስን የካደው ለምንድን ነው?
ጴጥሮስ የካደው ፈርቶ ስለነበር ነው።
133. በኢየሱስ ላይ ሞት ተፈረደ
ሉቃስ 22፥66 – 23፥25
በማለዳም ኢየሱሰን የእስራኤል መሪዎች ለፍርድ አቀረቡት። በዚያም ብዙ ጥያቄዎችን እየጠየቁ መረመሩት። ክፉ ነገር ባያድርግም፥ በውሸት ወንጀለኛ አደረጉት። ኢየሱስም በቅርብ* ጊዜ በእግዚአብሔር አጠገብ በዙፋን ላይ እንደሚቀመጥ ነገራቸው። በዚህ ምክንያት “እግዚአብሔርን ሰደበ” ብለው ወደ ሮም መንግሥት ተወካዮች ወሰዱት። በእነርሱም ፊት ኢየሱስን ደግመው ከሰሱት። ሆኖም እነርሱም ምንም ዐይነት ጥፋት አላገኙበትም። ኢየሱስ ግን በሁሉም ፊት እንደ በግ ዝም አለ። ምክንያቱም እርሱ ለሰው ልጅ ኃጢያት ሁሉ የተዘጋጀ የእግዚአብሔር በግ ነው። በመጨረሻም አብዘኞቹ መሪዎች በአንድነት ኢየሱስ መሞት እንዳለበት ተስማሙ።
Jesus Sentenced to Death
Luke 22:66 – 23:25
Early in the morning, the leaders of Israel put Jesus on trial. They asked him many questions to find a reason on which to condemn him. And even though he had not done anything evil, they treated him like a criminal. Regardless, Jesus told them that he would soon sit on the throne next to God. Because he had said this, they declared, “He has insulted God!” and took him to the rulers of the Roman government to accuse him there also. But these rulers didn’t find any guilt in him. He was quiet like a lamb in front of them all. He really is the Lamb of God, who was prepared to die for the sin of all people. In the end, most of the leaders agreed that Jesus had to die.

የእስራኤል መሪዎች ኢየሱስን መሞት እንዳለበት በሮም መንግሥት ተወካይ ፊት ሲከሱት
ኢየሱስ የተከሰሰው ጥፋት አጥፍቶ ነበር?
አይደለም፥ ምንም ጥፋት አላደረግም።
134. ኢየሱስ በመስቀል ላይ ሞተ
ሉቃስ 23፥33-49 + ማቴዎስ 27፥33-56
ከዚያ በኋላ ወታደሮች ኢየሱስን ይዘውት ከከተማ ወጡ። በሁለት ወንጀለኞች መካከል በመስቀል ላይ እጁን እና እግሩን በምስማር አጣብቀው ሰቀሉት። ከወንጀለኞቹ አንዱ በኢየሱስ ላይ መጥፎ ንግግር ተናገረ። ሌላኛው ግን ኃጢአተኛ መሆኑን አውቆ በሚመጣው መንግሥቱ ምሕረት እንዲያደርግለት ጠየቀው። ኢየሱስም ወንጀለኛውን ይቅርታ አድርጎለት “ዛሬ ከእኔ ጋር በሰማያዊ ስፍራ ትሆናለህ” አለው።
ኢየሱስ በተሰቀለ ጊዜ ከቀኑ 6 ሰዓት እስከ 9 ሰዓት ድረስ ጨለመ። በመስቀልም ላይ እያለ ሞተ። በዚህ ጊዜ መሬት ተንቀጠቀጠ፥ እንዲሁም ወደ ቤተ መቅደስ ውስጠኛ ክፍል መግቢያ የነበረው መጋረጃ ከላይ ወደታች ተቀደደ። ይህ የሚያሳየው በኃጢያት ምክንያት ዝግ የነበረው ወደ እግዚአብሔር የሚወስደው መንገድ ለሁሉም ሰው መከፈቱን ነው።
Jesus’ Death on the Cross
Luke 23:33-49 + Matthew 27:33-56
After that, some soldiers took Jesus out of the city. There they nailed him to a wooden cross between two criminals. One of the two mocked Jesus. But the other one was aware of his sin and asked Jesus to have mercy on him in his coming kingdom. Jesus forgave him and answered, “Today you will be with me in the heavenly place, in paradise!”
On that day, at lunch time at 12 o’clock, the sky became dark for 3 hours. Then Jesus died on the cross. There was an earthquake at the time of his death. And also the curtain to the most holy place in the Temple tore apart from top to bottom. This shows that the way to God opened up for everyone. It had been closed because of sin.

ኢየሱስ ምንም ጥፋት ሳይኖርበት ስለእኛ ኃጢያት በመስቀል ላይ ሲሞት
ኢየሱስ በመስቀል ላይ ሲሞት የትኛው መንገድ ተከፈተ?
ወደ እግዚአብሔር የሚወስደው መንገድ ተከፈተ።
135. ኢየሱስ ከሞት ተነሳ
ማቴዎስ 27፥57 – 28፥10
ኢየሱስ ከሞተ በኋላ፥ እርሱን በድብቅ ይከተል የነበረ መልካም ሰው፥ አስከሬኑን ወስዶ በአዲስ መቃብር ውስጥ አስቀመጠው። ይህ የሆነው አርብ ከሰአት በኋላ ነበር። ቅዳሜ የእረፍት ቀን ስለነበር፥ ማንም ሰው ወደ መቃብር አልሄደም። እሁድ በማለዳ አንዳንድ ሴቶች የኢየሱስን አስከሬን ሽቶ ሊቀቡ ወደ መቃብር ቦታ ሄዱ። በመቃብሩም ቦታ መልአክ ተገለጠ። በዚህ ምክንያት መሬቱ* ተንቀጠቀጠ፥ የኢየሱስ መቃብር የተዘጋበት ትልቅ ድንጋይም ተንከባለለ፥ እንዲሁም መቃብሩን ሲጠብቁ የነበሩ ጠባቂዎች በፍርሀት እንደሞተ ሰው ሆነው ወደቁ።
በዚህ ጊዜ መልአኩ ለሴቶቹ “አትፍሩ! ኢየሱስ አስቀድሞ እንደተናገረ ከሞት ተነስቷል። ቶሎ ሄዳችሁ ለተከታዮቹ ይህንን የምስራች ንገሯቸው!” አላቸው። ሴቶቹም ኢየሱስ በመቃብሩ ውስጥ እንደሌለ አዩ። በፍጥነትም ወደ ኢየሱስ ተከታዮች ሄዱ። በመንገድም እያሉ ኢየሱስ በድንገት ታያቸው። ስለዚህ በደስታ ተሞልተው መልካሙን ዜና ለተከታዮቹ ተናገሩ። እነርሱም በጣም ተገረሙ። ወዲያውኑ ግን አላመኗቸውም ነበር።
Jesus Rises From Death
Matthew 27:57 – 28:10
After Jesus died, a good man who was a secret follower of Jesus, took his dead body and put it in a new grave. This happened on Friday afternoon. Nobody went to the grave on Saturday, because it was the day of rest. But early on Sunday morning a few women went there in order to put oil on the corpse. Then there was an earthquake, for an angel appeared at the grave. He rolled aside the big stone that had closed it off. And the guards who had been guarding the grave fainted with fear.
The angel said to the women, “Don’t be afraid! Jesus has risen from the dead just as he told you before. Quickly go and tell his disciples about this!” And the women saw that the grave was empty. On their way back, Jesus suddenly met them. They were so happy because of this. Full of joy they told the disciples the good news. The disciples were really amazed, but did not believe them immediately.

በመቃብር ቦታ ጠባቂዎቹ በፍርሀት ወድቀው፥ መልአኩ ለሴቶች “ኢየሱስ ተነስቷል” ሲላቸው
ሴቶቹ ኢየሱስን በመቃብር ውስጥ ለምን አላገኙትም?
በመቃብር ውስጥ ያላገኙት፥ ኢየሱስ ከሞት ስለተነሳ ነው።
136. ኢየሱስ ለተከታዮቹ ታየ
ሉቃስ 24፥36-43
ከዚህም በኋላ ኢየሱስ ለተከታዮቹ ታየ። እነርሱም በመጀመሪያ ሲያዩት፥ የሞተ ሰው መንፈስ መሰሏቸው ነበር። ኢየሱስ ግን በእውነት ከሞት ተነስቶ እንጂ፥ መንፈስ አልነበረም። ስለዚህ በእግሮቹ፥ በእጆቹ እና በጎኑ ላይ የነበረው ቁስሎችን አሳያቸው። እንዲያምኑም በእጃቸው እንዲነኩት ጠየቃቸው። በተጨማሪም በፊታቸው የተጠበሰ ዓሣ በላ። ይህን ሁሉ ባዩ ጊዜ በእውነት ኢየሱስ ከሞት እንደተነሳ አወቁ። በዚህም ምክንያት በደስታ ተሞሉ።
Jesus Appears to His Disciples
Luke 24:36-43
Afterwards Jesus appeared to his followers. When they first saw him, they thought they were seeing the spirit of a dead person. However, Jesus was not a ghost. He really had risen from death. He showed them the wounds on his feet, his hands and his side. And he asked them to even touch him so that they would believe it. In addition he ate some fish in front of their eyes. When the disciples saw all this, they knew for sure that Jesus had risen from death. And they rejoiced greatly!

ተከታዮቹ ኢየሱስ ከሞት ከተነሳ በኋላ ሲያገኙት
ተከታዮቹ ለምን በደስታ ተሞሉ?
ኢየሱስ ከሞት ስለተነሳ በደስታ ተሞሉ።
137. ኢየሱስ ጴጥሮስን ሾመው
ዮሐነስ 21፥1-17
አንድ ሌሊት ጴጥሮስ ከአንዳንድ ሐዋርያት ጋር ዓሳ ለማጥመድ ሄደ። ሌሊቱን ሙሉ ግን ምንም ዓሳ አልያዙም። በማለዳም በሐይቁ ዳርቻ ኢየሱስን ቆሞ አዩት። ማን እንደሆነ ግን ገና አላወቁም ነበር። ኢየሱስም “ከጀልባው በቀኝ በኩል መረቡን ጣሉት። ዓሳም ታገኛላቸሁ” አላቸው። እርሱም እንዳላቸው ባደረጉ ጊዜ፥ ጀልባዋ መያዝ እስከማትችል ድረስ ብዙ ዓሳ ያዙ። ከዚህም በኋላ በባሕሩ ዳር የቆመው ሰው ኢየሱስ መሆኑን አወቁ።
ኢየሱስም በእሳት ላይ ዓሣ ጠብሶ በዳቦ አበላቸው። እነርሱም ምግብ ከበሉ በኋላ፥ ጴጥሮስን አነጋገረው። ጴጥሮስ ስህተት ያለበት ሰው ቢሆንም፥ ኢየሱስን ግን ይወደው ነበር። ስለዚህ ለተከታዮቹ ጥሩ እረኛ እንዲሆን ሾመው።
Jesus Assigns Peter
John 21:1-17
One night Peter and some other disciples went out to catch fish. But they didn’t catch any fish all night long. In the morning they saw Jesus standing at the shore of the lake. But they didn’t know who he was. He told them, “Throw out the net on the right side of the boat, and you will catch fish.” When they did what he said, they caught more fish than they were able to put into the boat. Then they realised that the person on the shore was Jesus.
He had already prepared some fish and bread on a fire for them to eat. After they had eaten breakfast, Jesus talked with Peter. Peter was a person who made mistakes, but he loved Jesus. For this reason Jesus assigned him the task to be a good shepherd for his followers.

ኢየሱስም በሐይቅ ዳር ለሐዋርያት ቁርስ አዘጋጅቶ በድጋሜ ሲታያቸው
ኢየሱስ ወደ ሰማይ ከመሄዱ በፊት ለተከታዮቹ ማንን መሪ እንዲሆን ሾመ?
ጴጥሮስን መሪ እንዲሆን ሾመው።
138. ሄዳችሁ መልካሙን መልእክት ተናገሩ!
ሉቃስ 24፥44-49
ኢየሱስ ከሞት ተነስቶ ወደ ሰማይ ከመሄዱ በፊት ለመጨረሻ ጊዜ ለተከታዮቹ ስለ እግዚአብሔር ቃል አስተማራቸው። በትምህርቱም ይመጣል ብለው ሲጠበቁት የነበረው አዳኝ እርሱ እንደሆነ አስረዳቸው። በተጨማሪም ሞቶ ከሞት መነሣትም እንደነበረበት ገለጸላቸው። በዚህ መንገድ እንጂ፥ ሰዎችን ለማዳን ሌላ አማራጭ አልነበረም። ነቢያትም ስለዚህ ጉዳይ ከብዙ መቶ ዓመታት በፊት ጽፈው ነበር።
ስለዚህ አሁን በኢየሱስ የሚታምኑ ሰዎች ሁሉ ከጥፋት መዳን ይችላሉ። እግዚአብሔርም ይቅር ሊላቸው ይፈልጋል። ኢየሱስ ተከታዮቹን ይህንን የእግዚአብሔር ምሕረትን የያዘ መልእክት ወደ ዓለም ሁሉ ሄደው፥ ለማንኛውም ሰው እንዲናገሩ አዘዛቸው።
Go and Share the Good News!
Luke 24:44-49
After his resurrection Jesus taught the disciples for a last time about the word of God before he went to heaven. In his teaching, he explained to them that he was the awaited Saviour and that he had to die and rise from the dead. There was no other way for him to save people. The prophets had already written about it hundreds of years before.
So now all people who trust Jesus can be saved. God wants to forgive them. Therefore, Jesus told his followers to go into the world and share this good news about God’s mercy with everyone.

ኢየሱስ ተከታዮቹን መልካሙን መልእክት ለሰዎች ሁሉ እንዲናገሩ ሲያዛቸው
የእግዚአብሔርን ምሕረት የያዘ የምሥራች ምንድን ነው?
በኢየሱስ የሚታምኑ ሰዎች ሁሉ ከጥፋት መዳን መቻላቸው ነው።
139. ኢየሱስ ወደ አባቱ ተመለሰ
የሐዋርያት ሥራ 1፥1-14 + ማቴዎስ 28፥16-20 + ዮሐንስ 14
ኢየሱስ “መንፈስ ቅዱስ ሲመጣ ይረዳችኋል፥ ያጽናናችኋል፥ ደግሞም ያስተምራችኋል” ብሎ አስቀድሞ አስተምሮ ነበር። በመጨረሻም ለተከታዮቹ
“በቅርብ ጊዜ መንፈስ ቅዱስን እልክላችኋለሁ። እርሱም ስለ አዳኝነቴ እና ምሕረቴ እንድትናገሩ ይረዳችኋል። ስለዚህ እርሱ እስኪመጣ ድረስ በኢየሩሳሌም ቆዩ!” ብሎ ነገራቸው።
ወደ ሰማይም ከመሄዱ በፊት “ሁልጊዜ ከእናንተ ጋር እሆናለሁ” አላቸው። ከዚያም ኢየሱስ እጆቹን አንሥቶ ባረካቸው። እነርሱም እያዩት ሳለ ወደ ሰማይ ተወሰደ። ወደ አባቱም ወደ እግዚአብሔር ተመልሶ በጎኑ በዙፋን ላይ ተቀመጠ። እርሱ ለዘለአለም ጌታ ነው። ወደ ላይ እንደ ወጣ እንደዚሁ አንድ ቀን ወደዚህ ዓለም ተመልሶ ይመጣል።
ኢየሱስ ወደ ሰማይ ከሄደ በኋላ፥ ተከታዮቹ ወደ ኢየሩሳሌም ተመለሱ። እግዚአብሔርን እያመሰገኑ እና እየጸለዩ የመንፈስ ቅዱስን መምጣት እየጠበቁ ቆዩ።
Jesus Returns to His Father
Acts 1:1-14 + Matthew 28:16-20 + John 14
Jesus had been teaching earlier, “When the Holy Spirit comes, he will help, comfort and teach you.” Finally he also said to his followers, “I will soon send you the Holy Spirit. He will help you to speak about my salvation and mercy. Wait in Jerusalem until he comes!”
Before Jesus went to heaven, he said to his disciples, “I will always be with you!” Then he lifted up his arms and blessed them. He was taken up to heaven while they were watching. He returned to God – his Father. There he sat down beside him on the throne. He is LORD for all eternity. And one day he will come back to this world in the same way he left.
After Jesus went to heaven, his followers went back to Jerusalem. There they waited for the coming of the Holy Spirit while praising God and praying together.

ኢየሱስ ይህንን ዓለም ትቶ ወደ እግዚአብሔር አብ ሲመለስ
ኢየሱስ ወዴት ተወሰደ?
ኢየሱስ ወደ አባቱ ወደ ሰማይ ተወሰደ።
140. መንፈስ ቅዱስ
የሐዋርያት ሥራ 2፥1-12 + 1ኛ ቆሮንቶስ 12፥7
ከጥቂት ቀናት በኋላ የኢየሱስ ተከታዮች አብረው በአንድ ቦታ ሳሉ፥ መንፈስ ቅዱስ መጣ። በዚህ ጊዜ በድንገት ከሰማይ ኃይለኛ የሆነ የነፋስ ድምፅ ሰሙ። ደግሞ በእያንዳንዳቸው ላይ ትናንሽ እሳት የሚመስል ነበልባል ተቀመጠባቸው። ነገር ግን አላቃጠላቸውም። ምክንያቱም የእግዚያብሔር መንፈስ የተሰጠው ሰውን ሊረዳ እንጂ፥ ሊጎዳ አይደለም። ወዲያውም በማያውቁት በተለያዩ ሀገር ሰዎች ቋንቋ መናገር ጀመሩ። እነዚህን ቋንቋዎች እንዲናገሩ የእግዚአብሔር መንፈስ ሰጥቷቸው ነበር። ከተላያዩ ሀገራት የመጡ ሰዎችም በሚያውቁት ቋንቋ ስለ እግዚአብሔር ስራ ሲናገሩ ሰምተው ተገረሙ።
ከዚህም በኋላ በመንፈስ ቅዱስ ኃይል እና ስጦታ በተሻለ ሁኔታ እርስ በርሳቸው መተናነጽ እና መረዳዳት ቻሉ። የመንፈስ ቅዱስ ኃይል ለራሳቸው ክብር ሳይሆን፥ ለእግዚአብሔር ክብር የተሰጠ ነው።
The Holy Spirit
Acts 2:1-12 + 1 Corinthians 12:7
A few days later while Jesus’ followers were all together in one place the Holy Spirit came. Suddenly they heard the noise of a strong wind. And something that looked like little flames of fire came to rest on each of them. But it didn’t burn them, for God’s Spirit was given to help people, not to hurt them. When the Spirit came, Jesus’ followers suddenly started to talk in various languages of other nations. They had never learned these languages, but God’s Spirit had given them the ability to speak them. People who had come from other countries were surprised to hear them speak about the great things God had done, each one in their own language.
After this Jesus’ followers were able to build each other up and help each other better. The power and the gift of the Holy Spirit enabled them to do so. His power is not given to bring honour to people, but to bring glory to God.

የእግዚአብሔር መንፈስ ወደ ክርስትያኖች ሲመጣ
የእግዚአብሔር መንፈስ ሰዎችን ይጎዳል?
መንፈስ ቅዱስ ሰዎችን አይጎዳም።
የእግዚአብሔር መንፈስ ኃይል እና ስጦታ ለምን ይሰጣል?
እርስ በርሳችን ለመተናነጽ እና ለመረዳዳት ይሰጣል።
141. የጴጥሮስ ስብከት
የሐዋርያት ሥራ 2፥14-47
መንፈስ ቅዱስ ከመጣ በኋላ፥ ጴጥሮስ ሳይፈራ ለተሰበሰበው ሕዝብ ለመናገር ተነሳ። ለእነርሱም ይህ ያዩት እና የሰሙት አስደናቂ ነገር የመንፈስ ቅዱስ መምጣት እንደሆነ አስረዳቸው። ኢየሱስም ሞትን አሸንፎ እንደተነሳ እና ሰው ሁሉ የሚድነው በእርሱ በማመን እንደሆነ አስተማረ። ይህንን የጴጥሮስ ስብከት የሰሙ ብዙ ሰዎችም በኢየሱስ አምነው ተጠመቁ።
በኢየሱስም ያመኑ ሰዎች አብረው በመጸለይ እና አንድ ለይ በመብላት በሰላም ይኖሩ ነበር። ያላቸውን ገንዘብ በአንድ ላይ ስላደረጉ ችግረኛ በመካከላቸው አልነበረም። እርስ በርሳቸውም በደስታ በጣም ይረዳዱ ነበር። ይህንን መልካም ስራቸውን ህዝቡ ስላዩ፥ በፊታቸው ሞገስን አገኙ።
Peter’s Sermon
Acts 2:14-47
After the Holy Spirit had come, Peter boldly got up to talk to the people who had gathered there. He explained to them that the amazing things which they had just seen and heard was the coming of the Holy Spirit. He also taught that Jesus rose, conquered death and saves everyone who believes in him. Many of the people who heard Peter’s sermon believed in Jesus and were baptised.
The Christians lived in peace with each other, praying and eating together. Because they shared the money they had, there was no needy person among them. Joyfully they helped each other. And so they gained the people’s goodwill due to their kind and generous actions.

ጴጥሮስ ለሕዝቡ የእግዚአብሔርን ቃል ሲያስተምር
ኢየሱስ የሚያድነው ማንን ነው?
የሚያድነው በእርሱ የሚያምንን ሰው ሁሉ ነው።
142. ጴጥሮስ እና ሽባው ሰው
የሐዋርያት ሥራ 3
በኢየሩሳሌም ሰዎች ሁሉ የሚያውቁት ከመወለዱ ጀምሮ ሽባ የሆነ አንድ ሰው ነበር። በየቀኑ በቤተ መቅደስ መግቢያ ተቀምጦ ገንዘብ ይለምን ነበር። አንድ ቀን ጴጥሮስ ባየው ጊዜ “የምሰጥህ ገንዘብ የለኝም። ነገር ግን በጌታ በኢየሱስ ስም ተነሳ እና ተራመድ!” አለው። ሽባውም ሰው ወዲያውኑ ተፈውሶ መራመድ ጀመረ። እየዘለለም እግዚአብሔርን በደስታ አመሰገነ። በዚህ ምክንያት ብዙ ሰዎች በጴጥሮስ እና በተፈወሰው ሰው ዙሪያ ተሰበሰቡ። በዚህ ጊዜ ጴጥሮስ ሽባውን የፈወሰው ኢየሱስ እንደሆነ በማስረዳት ክብርን ሁሉ ለእርሱ ሰጠ። ደግሞም ኢየሱስ አዳኝ እንደሆነ ነገራቸው።
Peter and the Paralyzed Man
Acts 3
There was a man in Jerusalem who was paralyzed from birth. Everyone knew him. He was begging for money at the entrance of the temple every day. One day when Peter saw him, he said to him, “I cannot give you money. Instead, in the name of the Lord Jesus, get up and walk!” And the paralysed man was healed immediately and started to walk. He praised God, jumping around full of joy. As a result many people gathered around Peter and the man who had been healed. Then Peter explained to them that it was Jesus who had healed the man and so gave him all the glory. He also told them that Jesus is the Saviour.

ጴጥሮስ ለሽባው በኢየሱስ ስም እንዲነሳ ሲነግረው እና ኢየሱስ ሲፈወሰው
ሽባውን ሰው ማን ፈወሰው?
የፈወሰው ኢየሱስ ነው።
143. ፊልጶስ እና የኢትዮጵያ ሰው
የሐዋርያት ሥራ 8፥26-40
ፊልጶስ የእግዚአብሔር ሰው ነበር። አንድ ቀን እግዚአብሔር ወደ ደቡብ እስራኤል እንዲሄድ ነገረው። ስለዚህ ፊልጶስ ወደዚያ ሄደ። በመንገድም እየሄድ ሳለ በጋሪ-ፈረስ ላይ አንድ ሰው አየ። እርሱም ከኢትዮጵያ እግዚአብሔርን ለማምልክ የመጣ የመንግሥት ባለሥልጣን ነበር። በመንገድም እያለ በነቢዩ ኢሳይያስ ስለ እግዚአብሔር በግ የተጻፈውን ክፍል እያነበበ ነበር። የተጻፈው ግን ስለምን ጉዳይ እንደሚናገር ግልጽ አልሆነለትም። ፊልጶስም ይህንን ሲያነብ በሰማው ጊዜ ቀርቦ አስረዳው። ኢየሱስ የእግዚአብሔር በግ እንደሆነ እና ከጥፋት ሁሉ ነፃ እንደሚያወጣ አስተማረው። ኢትዮጵያዊው ይህን ሰምቶ በኢየሱስ አምኖ ተጠመቀ። ከዚያ በኋላ ፊልጶስ በመንፈስ ቅዱስ ኃይል ወዲያውኑ ተወስዶ በሌላ ቦታ ታየ። ባለሥልጣኑ ግን በደስታ ወደ ኢትዮጵያ ተመለሰ።
Philip and the Ethiopian
Acts 8:26-40
Philip was a man of God. One day God told him to walk towards the southern part of Israel. And so he went there. As he was walking, he saw a man in a horse carriage. That man was a very important government official from Ethiopia who had come to Israel to worship God. On his way home, he was reading the part which the Prophet Isaiah wrote about the Lamb of God. But it was not clear to him what it was all about. When Philip heard him reading, he went closer and explained it to him. He taught him that Jesus is that Lamb of God and that he sets us free from any guilt. When the Ethiopian heard this, he believed in Jesus and was baptised. After that Philip was suddenly taken away by the power of the Holy Spirit and appeared in a different place. But the official joyfully went back to Ethiopia.

ፊልጶስ ከኢትዮጵያዊው ሰው ጋር ስለ ኢየሱስ ሲነጋገር
እግዚአብሔር ፊልጶስን ወደ ኢትዮጵያዊው የላከው ለምንድን ነው?
እግዚአብሔር የላከው ኢየሱስ አዳኝ እንደሆነ እንዲነግረው ነው።
144. ኢየሱስ እና ሳውል
የሐዋርያት ሥራ 9
ሳውል እግዚአብሔርን ትክክል ባልሆነ ሐሳብ ለማገልገል በጣም የሰራ ሰው ነበር። ስለዚህ የኢየሱስ ተከታዮችን የተሳሳተ መንገድ የሚከተሉ ስለመሰለው አሳደዳቸው። በሳውልም ምክንያት ብዙ ክርስትያኖች ከኢየሩሳሌም ሸሽተው ወጡ።
አንድ ቀን ሳውል ክርስትያኖችን ለማሳደድ ወደ ሌላ ከተማ ይሄድ ነበር። በመንገድ ላይ እያለ ኢየሱስ ተገልጦ አስቆመው። ሳውልም በድንገት በዙርያው ታላቅ ብርሃን ሲያንፀባረቀበት ወደቀ። ኢየሱስን “ሳውል! ለምን ታሳድደኛለህ?” ሲል ሰማው። ከዚህ በኋላ ሳውል ከመሬት ሲነሳ ዓይኖቹ ታውረው ነበር። ከሦስት ቀን በኋላ እንዲጸልይለት እግዚአብሔር ከክርስቲያኖች አንዱን ወደ ሳውል ላከ። የመጣው ሰው ከጸለየለት በኋላ፥ እንደገና ማየት ቻለ።
በዚህ መንገድ የሳውል ሕይወት ተለውጦ የኢየሱስ ተከታይ ሆነ። ስሙም ከዚያን ጊዜ ጀመሮ ጳውሎስ ተባለ።
Jesus and Saul
Acts 9
Saul was a man who worked very hard for God but with the wrong understanding. Therefore, he persecuted people who followed Jesus. He did so because he thought they were mistaken. Because of him many believers fled from Jerusalem.
One day Saul was going to another city to persecute Christians when Jesus appeared to him on the road and stopped him. Suddenly a big light shone around him and he fell to the ground. He heard Jesus’ voice say to him, “Saul, why are you persecuting me?” And afterwards, when Saul got up, he was blind. Three days later God sent one of the Christians to him in order to pray for him. And after that man had prayed for Saul, he was able to see again.
In this way Saul’s life was changed and he became a follower of Jesus. From then on his new name was Paul.

ኢየሱስ ለሳውል ተገልጦ ሲያስቆመው
ሳውል ከማን ጋር ስለተገናኘ ተለወጠ?
የተለወጠው ከኢየሱስ ጋር ስለተገናኘ ነው።
145. ጳውሎስ ስለ ኢየሱስ አስተማረ
የሐዋርያት ሥራ 9 + ተጨማሪ ምዕራፎች
ጳውሎስ ኢየሱስ የእግዚአብሔር ልጅ እንደሆነ ከተረዳ በኋላ፥ መኩራብ በሚባለው በእስራኤላውያን የጸሎት ቤቶች ስለ ኢየሱስ መስበክ ጀመረ። በተጨማሪም ወደ ሩቅ ሀገሮች በመሄድ ሌሎች ሕዝቦችን አስተማረ። አንዳንዶች ስለ ኢየሱስ ሲያስተምር፥ በደስታ ይሰሙት እና በኢየሱስ ያምኑ ነበር። አንዳንድ ሰዎች ግን የእርሱን መልእክት መስማት ስላልፈለጉ ተቃወሙት። እርሱ ግን አገልገሎቱን አላቆመም። በእግዚአብሔርም ኃይል ብዙ ተአምራትን አደረገ። በዚህም ብዙ ሰዎች እግዚአብሔር እንደሚወዳቸው እና የእግዚአብሔር ቃል እውነት እንደሆነ አወቁ።
Paul Teaches About Jesus
Acts 9 et al.
After Paul realised that Jesus is the Son of God, he started to teach about him at the synagogues. These are Israelite prayer houses. Additionally, he traveled to distant countries in order to teach people from other nations as well. Some people were glad to learn about Jesus and decided to follow him. But others opposed Paul, because they didn’t want to hear his message. Even so, he did not give up serving. He also did many miracles by the power of God. In this way many people were able to see that God loves them and that his word is true.

ጳውሎስ የእግዚአብሔርን ቃል ሲያስተምር
ጳውሎስ ጎበዝ አስተማሪ ነበር። ስለ ማን ነው ያስተማረው?
ስለ ኢየሱስ ክርስቶስ አስተማረ።
146. ጴጥሮስ ያየው ራእይ
የሐዋርያት ሥራ 10
አንድ ቀን ጴጥሮስ እየጸለየ ሳለ፥ ከእግዚአብሔር ራእይ አየ። ይህም ራእይ ሕልም የሚመስል እንቅልፍ ሳይተኛ የሚታይ ነው። በዚህም ራእይ ጴጥሮስ ከሰማይ የወረደ ጨርቅ አየ። ለእስራኤላውያን ለመብላት ያልተፈቀዱ እንስሳትን የተሞላ ጨርቅ ነበር። ቢሆንም፥ ከሰማይ አንድ ድምፅ እንሰሳቱን አርዶ እንዲበላ ነገረው። ጴጥሮስ ግን “ርኩስ እንሰሳትን አልበላም” ብሎ ሲመለስ፥ ወዲያው ድምፁ “እግዚአብሔር ንጹሕ ያደረገውን ርኩስ ነው አትበል” ብሎ ተናገረው። ጴጥሮስም ይህንን ራእይ ሦስት ጊዜ አየ። የዚህ ራእይ ትርጉም ማንንም ሰው እርኩስ እንዳይል ሲሆን፥ ደግሞም ስለ ኢየሱስ ለሰዎች ሁሉ እንዲናገር መሆኑን በመጨረሻ ተረዳ። ልክ በዚያን ሰዓት እንግዶች ወደ ሚኖርበት ቤት መጡ እና ከእነርሱ ጋር ወደ ቤታቸው እንዲሄድ ጠየቁት። እንግዶቹ ግን እስራኤላውያን አልነበሩም። ሆኖም ግን ጴጥሮስ እነርሱን መቀበል እንዳለበት እግዚአብሔር አስቀድሞ በራእዩ ግልጽ አድርጎለት ነበር።
ስለዚህ ወደ ሚኖርበት ቤት ጋበዛቸው። አብረውም ከበሉ በኋላ፥ ከእነርሱ ጋር ሄደ።
Peter’s Vision
Acts 10
One day while Peter was praying, he saw a vision from God. Such a vision is like dreaming without actually sleeping. In this vision, Peter saw a sheet which came down from heaven. It was full of animals that people from Israel were not allowed to eat. Yet a voice from heaven told him to slaughter and eat them. When Peter answered, “I won’t eat unclean animals,” he heard the voice say, “Don’t call anything unclean that God has made clean!” Peter saw this vision three times. In the end he understood that the vision meant he should not call any person unclean. It also meant he should tell people of any nationality about Jesus. Right at that moment, some strangers arrived at the house where he stayed and asked him to come with them. They were not from Israel. However, through the vision God had made it clear that Peter should accept them. So he invited them into the house where he stayed. And after they ate together, he went with them.

እግዚአብሔር ለጴጥሮስ ራእይ ሲያሳየው
እግዚአብሔር ሰዎች ሁሉ እንዲድኑ ይፈልጋል?
አዎን፥ ሰዎች ሁሉ እንዲድኑ ይፈልጋል።
147. ጴጥሮስ እስራኤላውያን ላልሆኑት ሰበከ
የሐዋርያት ሥራ 10
ጴጥሮስ ከመጡት እንገዶች ጋር ሮማዊ በሆነው ሰው ቤት ደረሰ። ይህ መልካም ሮማዊ ሁልጊዜ የሚፀልይ እና እግዚአብሔርን የሚያክብር ሰው ነበር። ነገር ግን ኢየሱስ አዳኝ እንደሆነ ገና አላወቀም ነበር። ሰውየውም የጴጥሮስን መልእክት አንድ ላይ እንዲሰሙ ዘመዶቹን ጋበዛቸው። ጴጥሮስም ለተሰብሰቡት ሰዎች ኢየሱስ አዳኝ እንደሆነ አስተማራቸው። እያስተማረም ሳለ፥ እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስን ለእነርሱም ደግሞ ሰጣቸው። ይህ ከሆነ በኋላ እነርሱን ለማጥመቅ መወሰን ከባድ አልነበረም። ስለዚህ ሮማዊው እና ዘመዶቹ ተጠመቁ።
ነገር ግን በኢየሩሳሌም የነበሩ እስራኤላዊ ክርስቲያኖች ይህንን ሲሰሙ ጴጥሮስን ተቃወሙት። በዚህ ምክንያት ጴጥሮስ እግዚአብሔር እርሱን እንዴት እስራኤላዊ ወዳልሆኑትን እንደመራው አስረዳቸው። እርሱም “እግዚአብሔር መንፈሱን ለእኛ ስጥቶ እንደነበር ለእነዚህም ሰዎች ሰጣቸው” ብሎ ገለጸላቸው። እግዚአብሔር እስራኤላዊ ያልሆኑትንም ደግሞ ሊያድን እንደወደደ ከተረዱ በኋላ፥ በመጨረሻ እግዚአብሔርን አመሰገኑ።
Peter Preaches to Non-Israelites
Acts 10
Together with the people that had come to him, Peter arrived at the house of a Roman man. This Roman was a good man who honoured God and prayed every day. But he didn’t know yet that Jesus is the Saviour. He had invited his relatives to hear what message Peter would have for them. So Peter taught the people gathered there that Jesus is the Saviour. And as he was teaching, God gave his Holy Spirit to them as well. After this happened, it was not difficult to decide to baptise these people who didn’t belong to Israel. And so the Roman man and his relatives were baptised.
However, when the Israelite believers in Jerusalem heard about this, they opposed Peter. Therefore, Peter helped them to understand how God had led him to the non-Israelites. He explained to them, “God has given his Spirit to them just as he gave to us” After they had come to realise that God wants to save non-Israelites as well, they praised God.

ሮማዊው ሰው በጴጥሮስ ፊት ሲሰገድ እና ጴጥሮስ ይህንን ሲከለክለው
እግዚአብሔር ወንጌልን ለማንኛውም ሰው እንድንናገር ይፈልጋል?
አዎን፥ እግዚአብሔር ሰውን ሁሉ ስለሚወድ ለማንኛውም ሰው ወንጌልን እንድንናገር ይፈልጋል።
148. ጴጥሮስ ከእስር ቤት ነፃ ወጣ
የሐዋርያት ሥራ 12
ሄሮድስ የሚባል ንጉሥ አንዳንድ ክርስትያኖችን ምንም ሳያጠፉ ማሰር ጀመረ። ጴጥሮስንም እስር ቤት አስገባው። እርሱም በወፍራም ሰንሰለት ታስሮ፥ በብዙ ጠባቂዎች ይጠበቅ ነበር። በዚህ ጊዜ ክርስትያኖች ተሰብስበው ለጴጥሮስ በጣም ይጸልዩ ነበር። ጴጥሮስ በእስር ቤት እንዳለ፥ በሌሊት ድንገት አንድ መልአክ ወደ እርሱ መጣ። ተነሥቶም ወደ ውጭ እንዲከተለው ነገረው። የታሰረበትም ሰንሰለቶች ተፈተው ከላዩ ወደቁ። የእስር ቤቱ በሮችም በተአምር ተከፈቱ። በዚህ ጊዜ ጴጥሮስ ሕልም የሚያይ መስሎት ነበር። ነገር ግን ከእስር ቤት ውጭ በነበረበት ጊዜ በእውነት ነጻ መሆኑን ተረዳ። ከዚያም ሲፀልዩለት ወደ ነበሩት ወገኖች ሄደ። ጴጥሮስንም ባዩት ጊዜ በጣም ተገረሙ። እንደገና ስላዩትም እግዚአብሔርን አመሰገኑ።
ጴጥሮስ ካረጀ በኋላ፥ ስለ ኢየሱስ ብዙ መከራ ተቀበለ። ቢሆንም ሁልጊዜ እግዚአብሔር ከእርሱ ጋር ነበር።
Peter Freed from Prison
Acts 12
Some time later, King Herod started to imprison Christians, although they hadn’t done anything wrong. Peter was put in prison as well. He was bound with heavy chains and guarded by many guards. But the other believers had gathered and were praying seriously for him. So Peter was in this difficult situation when suddenly an angel came to him in the middle of the night. He told him to get up and follow him outside. Peter’s chains simply fell off and the prison doors miraculously opened. At that time it all seemed like a dream to Peter. But once he was outside the prison he realised that he really was free. Then he went to the believers who were praying for him. They were so amazed when they saw him. And they thanked God for bringing them back together.
Later in his life, Peter suffered a lot for Jesus. Yet, God was always with him.

ጴጥሮስን ከእስር ቤት ነፃ ለማውጣት የእግዚአብሔር መልአክ ሲያናግረው
ጴጥሮስ በእስር ቤት እያለ እግዚአብሔር ከእርሱ ጋር ነበር?
አዎን፥ እግዚአብሔር በእስር ቤትም ሆነ፥ በማንኛውን ጊዜ ከእርሱ ጋር ነበር።
149. የጳውሎስ መታሰር እና ደብዳቤዎቹ
የሐዋርያት ሥራ 13-28
ጳውሎስ ወደ ብዙ ሀገሮች እየተጓዘ ሰዎችን ስለ ኢየሱስ ማስተማሩን ቀጠለ። በየሄደበት ቦታም ሲያስተምር፥ ሰዎች በኢየሱስ ስላመኑ ብዙ ቤተ ክርስቲያናት ተመሰረቱ።
ከተወሰኑ ዓመታት በኋላ ጳውሎስን የሚቃወሙ ሰዎች ወደ እስር ቤት አስገቡት። ለፍርድም በዳኛ ፊት በቆመበት ጊዜ፥ ለአንዳንድ የመንግሥት መሪዎች ስለ ኢየሱስ ተናገረ። በመጨረሻም እስረኛ ሆኖ በመርከብ ወደ ሮም ከተማ ተጓዘ። ሆኖም ግን የነበረባት መርከብ በተነሳ ከባድ የንፋስ ማዕበል ተሰባበረች። እግዚአብሔር ግን ጳውሎስን እና በመርከቧ የነበሩትን ሰዎች ሁሉ ከጥፋት አዳናቸው። በመጨረሻም ጳውሎስ ሮም ደረሰ። በሮምም እስረኛ በነበረበት ጊዜ እንግዶችን እንዲቀበል ተፈቅዶለት ነበር። በዚያን ጊዜ ለተለያዩ ቤተ ክርስቲያናት መንፈሳዊ ሕይወት የሚጠቅሙ ብዙ ደብዳቤዎችን ጻፈ። ከእነዚህ ደብዳቤዎች ብዙዎቹ ለእኛም ሕይወት ጠቃሚ ስለሆኑ፥ በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ይገኛሉ።
Paul Writes Letters
Acts 13-28
Paul travelled to many countries and continued teaching people about Jesus. Everywhere he went, people decided to put their trust in Jesus, and many churches were established.
After a number of years, the people who opposed his teaching put him in prison. And when he was brought before the judge, he used the opportunity to explain the gospel to government leaders as well. Finally, he was taken by ship to the city of Rome as a prisoner. But due to a severe storm the ship he was travelling on broke apart and sank. However, God saved Paul and all the other people who were on the ship. In the end he arrived in the city of Rome. At the time he was a prisoner there, he was allowed to receive visitors. And during that period, he also wrote many letters that were helpful for the spiritual life of various churches. Many of his letters are part of the Bible because they are helpful for our spiritual life too.

ጳውሎስ በሮም እስረኛ በነበረበት ጊዜ እንግዶችን ሲቀበል
ጳውሎስ የፃፋቸው ደብዳቤዎች ለምን ይጠቅማሉ?
ለመንፈሳዊ ሕይወታችን ይጠቅማሉ።
150. ኢየሱስ እንደገና ይመጣል
የዮሐንስ ራእይ፥ ማቴዎስ 25
ሐዋሪያው ዮሐንስ ሰማይን፥ ማለትም እግዚአብሔር ያለበትን ቦታ በራእይ አየ። ይህ ቦታ በደስታ እና በፍቅር የተሞላ ውብ ቦታ እንደሆነ ተመለከተ። መንገዶቹም ከወርቅ የተሠሩ ናቸው። በሽታ፥ ሞት፥ ሐዘን፥ ውጊያ ወይም ሰይጣን እዚያ የለም። በዚያም ሰፍራ ያለው ንጉሥ ኢየሱስ ነው።
ዮሐንስም ያየውን ሁሉ በራእይ መጽሐፍ ውስጥ ጻፈ። በዚህም መጽሐፍ የተጸፉት ትንቢቶች መፈጸም ሲጀምሩ ለሰዎች ግልጽ እየሆኑ ይመጣሉ።
አሁንም ኢየሱስ የእግዚአብሔር በግ እና የነገሥታት ንጉሥ እንደሆነ እናውቃለን። እርሱ ከሌሎቹ ኀያላን ሁሉ ይበልጣል። እንደገናም ተመልሶ ወደ ምድር ይመጣል። ነገር ግን መቼ እንደሚመጣ ትክክለኛውን ጊዜ ማንም ሰው አያውቅም። ሲመለስ ግን በክፉ ሰዎች ላይ እንደሚፈርድ እናውቃለን። የእርሱ የሆኑት ልጆቹ ይህንን ፍርድ አይፈሩም። ይልቁንም አዳኛቸውን ሲያዩ በጣም ይደሰታሉ። የእግዚአብሔር በግ፥ ኢየሱስ ልጆቹን ይቀበላቸዋል እንጂ፥ አይፈርድባቸውም።
Jesus Will Come Again
Revelation + Matthew 25
The Apostle John saw a vision of heaven – the place where God is. He saw that it is a beautiful place full of joy and love. The roads there are made of gold. There is no sickness, no death, no sadness and no fighting. Satan isn’t there either. Jesus reigns there as king.
John wrote down everything he saw in the Book of Revelation. When the things described in this book start to happen, people will understand them more clearly.
We already understand now that Jesus is the Lamb of God and the King of Kings. He is stronger than any other power. He will come back to the earth. But no one knows when he will come exactly. Yet, we know that when he returns, he will judge evil people. But those who belong to him – his children – will not be afraid of this judgment. On the contrary, they will be very happy to see their Saviour. Jesus – the Lamb of God – will accept his children, and will not condemn them.
Even now, Jesus is always with his children.
አሁንም ቢሆን፥ ኢየሱስ ሁልጊዜ ከልጆቹ ጋር ነው።

ኢየሱስ የጌቶች ጌታ ሆኖ በክብር እና በኃይል ሲመለስ
ኢየሱስ እንደገና በክብር ሲመጣ ለማን ምሕረት ያደርጋል?
ኢየሱስ በእርሱ ለሚያምኑ ልጆቹ ምሕረት ያደርጋል።


ኣብ ታሪኽ 128-150 ድለዩ: